Saturday, June 10, 2017

3rd African cup of nation hosted by Ethiopia & Ethiopia won the tournament የ3ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኢትዮጵያ

መቅደላ አምባ የታሪክ ማህደር


               መቅደላ አምባ





«መቅደላ አፋፉ ላይ ጩ ከት በረከተ የሴቱን አናውቅም ወንድ አንድ ሰው ሞተ» የተባለላት መቅደላ አምባ ከአካባቢው ተራሮች በላይ እራሷን ጎፍራ ተቀምጣለች። የመቅደላ አምባ ዙሪያውን የሚገኙ ስፍራዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችል መልከአምድር የያዘ በመሆኑ ጦርነት ለመምራት መቺ እንደሆነ መገመት ይቻላል። የጻውሎስ ኞኞ አፄ ቴዎድሮስ መጽሃፍ እንደሚያትተው ከቦታው ጥንታዊ የብራና መጽሃፍት፣ የወርቅና ብር ዋንጫዎች፣ አክሊሎችና ሌሎች የአፄ ተዎድሮስ እና ንጉስ ሚካኤል ቅርሶች ከመቅደላው ጦርነትና ከአፄ ቴዎደሮስ እረፍት በኋላ በናፒዬር የተመራው የእንግሊዝ ጦር በግመል አስጭኖ ወደ አገሩ ወስዷቸዋል። በአሁኑ ጊዜም በእንግሊዝ አገር የተለያዩ መዘክሮች ውስጥ ተቀምጠው ከሚገኙ ቅርሶች ውጪ መድፎች እና የቤተመንግስቱ ፍርስራሶች በቦታው ይገኛሉ።


ታሪካዊው የመቅደላ አምባ ተራራማው በሆነው የአማራ ክልል ተንታ ወረዳ ውስጥ ይገኛል። ቦታው ለመድረስም ከደሴ ከተማ በስተምዕራብ አቅጣጫ 157ኪሎ ሜትር ርቀት መጓዝ ይጠይቃል። በቦታው እንግሊዞችን የተዋጉባቸው መድፎች መካከለል አንዱ በቆርቆሮ በተሸፈነ አጥር ተከልሎ ይገኛል። አጥሩ ዙሪያውን ሐረግ የወረሰው ሲሆን ጽዳት እንደሚያስፈልገው ያየው ሁሉ ይመሰክራል። አምባው ላይ ሲወጡ የአፄ ቴዎደሮስ እራሳቸውን ያጠፉበት ቦታ ተከለሎ ያገኙታል። በ2000 .ም የተገነባው መቃብራቸውም በአካባቢው ታሪክን ያወሳል። የንጉሱ እቃ ግምጃ ቤትና እንግሊዞች በርካታ ብራና መጻህፍትን የዘረፉበት የመቅደላ መድሃኒአለም ቤተክርስቲያንም ፍርስራሹ ብቻ በቦታው ይገኛል። በአካባቢው እንደ አስጎብኚም እንደ ጥበቃም ሆነው የታዩት የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው።

Featured post

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

                    የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደር...