Monday, March 12, 2018

Ethiopia: የአለላዋ ምድር


አዲስ አበባ ምስራቅ አቅጣጫ 500 ኪሎ ሜትሮችን ጓዙ የእራሳቸው ቀለማት ያላቸውን የሐረሪዎችን ከተሞች ያገኟቸዋልየሐረሪ ክልል መዲና ሐረርብዛኛው ስነህንፃ ውበቶቿ በተለይም በጀጎል ግንብ ታዋቂ ብትሆንም የክልሉ ባህላዊ አልባሳቶች መገልገያ ዕቃዎች እና በቤቶች ውስጥ ያረፉትን የዕደ ጥበብ ውጤቶች ደግሞ ከአዕምሮ ሊጠፋ የማይችል ትዝታን የየመፍጠር አቅም አላቸው።
ሐረሪዎች ጥንታዊ የዕደጥበብን ከቤተሰብ እየተቀባበሉ ያደጉ ናቸው:: የሐረሪ የዕደ ጥበብ ውጤቶች ለቤት ማስጌጫነት እና ለውበት ማድመቂያነት ይውላሉ:: በተለይ ስፌት ሙያ የሌላት ሴት ቤቷን ለማስጌጥ እና ባህሏን ለማከበር ያላት እድል ዝቅታ በመሆኑ ከዘመድ አዝማድም ሆነ ከጎረቤት ሙያውን ለመልመድ ከፍተኛ ጥረት ታደርጋለች::

የእደጥበብ ውጤቶች በተለይም የስፌት እና የማስዋቢያ እቃዎች በአንድ አካባቢ ውስጥ እንደባህል ተወስዶ የሚለመደው ማህበረሰቡ በአንድ ቦታ ተረጋግቶ መኖር ከጀመረ በኋላ ነው ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች:: ምክንያቱም የማስጌጫ እና የቅንጦት እቃዎችን ጥበብ ማስፋፋት የሚቻለው ለማህበረሰቡ አፈላጊ የሆኑ መሰረታዊ ጉዳዮችን ማሟላት ከተቻለ በኋላ መሆኑን እደ ማስረጃነት ያቀርባሉ:: ይህ አባባልም ሐረሪዎች የስፌት ጥበባቸውን እና ቤት ማስጌጫዎቻውን መስራት የጀመሩት ዘመናዊነት ከገባቸው እና ዘመናዊነትን ከተላመዱ ቆየት ያለ ጊዜ እዳስቆጠሩ ማሳያ ይሆናል::
የክልሉ ርዕሰ መዲናም ሀረር ከፍተኛ የስልጣኔ እድገት ደረጃ ላይ በደረሰችበት በ16ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት እና የንግድ ማዕከል በመሆን ግልጋሎት ሰጥታለች፡፡ ይህም የበርካታ ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች እንዲሁም ረቂቅ የእጅ ጥበብ ያረፈባቸው መገልገያዎች ባለቤት እንድትሆን አድርጓታል የሚሉ የታሪክ ምሁራንም በርካታ ናቸው፡፡ ከቤት አሰራሩ ጀምሮ እስከ ምንጣፋቸው ድረስ ለአይ በሚማርክ መልኩ ማዋቀርን ተክነውበታል::
ሪሪዎች መኖሪያ ብንነሳ የእጅ ጥበብ ምን ያህል ዋጋ እነዳለው መረዳት ይቻላል:: የሐረሪዎች ባህላዊ ቤት ጌይ ጋር ይባላል:: ቤቱን የአገሩን ባህል የማያውቅ ጥበበኛ ካልሆነ በቀር ማንኛውም የግንባታ ባለሙያ አሳምሮ ሊሰራው ያዳግተዋል:: በሐረሪዎች ጌይ ማለት ከተማ ሲሆን ጋር ማለት ደግሞ ቤት ነው:: ከፍቺው የምንረዳው ጌይጋር ማለት የከተማ ቤት እንደማለት ይሆናል:: ከተሜዎቹ ሐረሮች ደግሞ ቤቶቻቸው ግድግዳ ላይ በርከት ብለው የሚንጠለጠሉ የዕደጥበብ ወጤቶችን እንደማስጌጫነት ይጠቀማሉ::
የክልሉ ነዋሪ አቶ መሃመድ ካሊድ እንደሚሉትበወይን ጠጅ፣ቀይ፣ አረንጓዴ እና ሌሎችም ህብረ ቀለማት የተጌጡ ሰፌዶች፣ ኢራዝ ሙዳይ እና ሌሎች የስፌት አይነቶችም በሐረሪዎች ቤት የማይጠፉ የዕደጥበብ ውጤቶች ናቸው:: ሁሉም የየእራሳቸው አገልግሎት ቢኖራቸውም ከአገልግሎታቸው በተጨማሪ ግን ለውበት መገለጫነት እንዲያገለግሉ በሚል በስነውበት ደረጃቸው ከፍ እንዲል ተደርጎ ይዘጋጃሉ:: በመሆኑም ለዳቦ እና ቆሎ ማቅረቢያነት የሚውል የስፌት እቃ እንኳን በግድግዳ ላይ ቢቀመጥ ጀርባው ውብ ሆኖ ለሰው መታየት አለበትና በሐረሬዎች እጅ በጥልቅ ዲዛይን እንዲዋብ መደረጉ አይቀሬ ነው::
በአሁኑ ወቅት የሐረሪዎች የስፌቶቻቸው ቅርፅ እና ዲዛይን ስነ ውበት የላቀ ደረጃ ከመድረሱም ባሻገር የተለያዩ ጎብኚዎችን ቀልብ መሳብ እየቻለ ይገኛል:: በተለያዩ ቀለማት ደምቀው እና ተውበው የተሰናዱት የዕደ ጥበብ ውጤቶችን ለተመለከተም ሐረሪዎች ምን ያህል የቀላማትን ህብር የመጠቀም ችሎታቸው የላቀ መሆኑን እንዲረዳ ያስገድደዋል::
ዕደ ጥበባቱ ለሐረሪዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው:: ምክንያቱም አንድም ለመገልገያነት ሲጠቅማቸው በሌላ በኩል ደግሞ ለጌጥ እና ማስዋቢያነት ጥቅም ላይ ይውላል:: ከዚህ ባለፈ ግን ለህብረተሰቡ ተምሳሌትነት እና ምልክት ሆኖ በመቅረብ እያስተዋወቃቸው ይገኛል::
ከእደ ጥበብ ውጤቶቻቸው መካከል በውበቱ ትልቁን ስፍራ የሚይዘው አለላ ነው:: አለላ የሐረሪ ሴቶች አሳምረው የሚሰፉት የሳሎን ሞሰብ አይነት የዕደጥበብ ውጤት ነው:: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባህል ማዕከል የህዝብ ግንኙነት እና አለም አቀፍ ዳይሬከተሯ ወይዘሮ ሰብለ አበበ እንደሚሉት፣ የሐረሪዎች ሞሰብ ከሌሎቹ የአገሪቷ ክፍል ከሚሰሩት የተለየ በመሆኑ ተፈላጊነቱ እየጨመረ ይገኛል:: በህብረቀለማት ከማጌጡም በላይ ደግሞ አለላው ከገብስ አገዳ መሰራቱ ከሌሎቹ ተመራጭ እና የተለየ ለመሆኑ አይነተኛ ሚና አበርክቷል::
በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍላት የሚዘጋጁት መሶብ እና ሙዳዮች ከሰበዝ ወይም ስንደዶ ከተባለ የሳር ዝርያ የሚዘጋጁ ናቸው:: ነገር ግን የሐረሪዎቹ አለላ በጥንቃቄ በተዘጋጁ የገብስ ተረፈ ምርት የሚሰሩ በመሆኑ በዋጋም ውድ ናቸው:: በሐረሪ ባለሙያ ሴት የተሰፋ አለላ በአሁኑ ወቅት ከአራት እና አምስት ሺ ብር በላይ ያወጣል:: የማህበረሰቡ ዲዛይንም ተወዳጅ እና ለአይን የሚማርክ በመሆኑ በቤት ውስጥ እንደ ማስጌጫነትም ያገለግላል:: በመሆኑም ይህን የዕደጥበብ ውጤት በሰፊው በማስተዋወቅ ሴቶች በገቢ ደረጃ አቅማቸውን የሚያሳድጉበት የስራ መስክ ማድረግ ያስፈልጋል::
ሌላው የሐረሪዎች የእጅ ጥበብ ያረፈባቸው መታወቂያቸው የባላዊ አልባሳቶቻቸው ናቸው:: ጠይ ኢራዝ የሚባለው ባህላዊ ልብስ በጥቁር ጨርቅ ላይ በተለያዩ ዲዛይኖች የሚዋበው ነው:: የባህል ልብሱ ልክ እንደ ነጭ የሐበሻ የአገር ባህል ልብስ የእራሱ የሆኑ ባለሙያዎች አማካኝነት በአግባቡ ይዘጋጃል:: ነገር ግን የሚለብሱት ያገቡ እና የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑ ሰዎች ብቻ ናችው:: በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍላተ አገራት ላይ ያላገቡ ሰዎችን እና ያገቡ ሰዎች ለመለየት የጸጉር አቆራረጣቸው እንደሚመሰክረው ሁሉ በሐረሪዎች ዘንድም የትዳር እና የእዕሜ ሁኔታን ለመለያየት የሚያገለግል የባህል አልባስ ሆኖ እየተዘወተረ ይገኛል::
ልጃገረዶች እና ሙሽሮች ደግሞ አጥላስ የተሰኘውን ባህላዊ ልብስ ይዋቡበታል:: ባህላዊ ልብሱ ደማቅ ቀለማትን የያዘ ሲሆን በአብዛኛው ጊዜም ለስላሳ ሆኖ በአረንጓዴ እና ቀይ ቀለማት ባላቸው ጨርቆች ይዘጋጃል:: በተለይ በጥልቅ የጥልፍ ዲዛይን እና በአበባ ቅርጽ የተጠለፉ ወርቃማ ክሮች ያሉበት ልብስ በመሆኑ በሰርግ ወቅት ሙሽሪት እና ሚዜዎቿ ተውበው ህዝብ ፊት ሲቀርቡበት ሐረሪዎች ውብ ባህል እንዳላቸው ምስክር የመሆን አቅም አለው::
ወንዶቹ በጌይ ከሎይታ ወይም ነጭ ኮፍያ መዋብ ከፈለጉ በባህላቸው የተዘጋጀ ቆብ ይዘጋጅላቸዋል:: ኮፍያዎቹ በብዛት ከክር የሚሰሩትን እና ለየት ባለ የስነ ውበት ደረጃ የተዘጋጁ ሲሆኑ ወንዶችም ከሐይማኖትም ሆነ ከባህል አንፃር በጭንቅላታቸው ላይ በማድረግ በከተማዋ ሲዘዋወሩ ይታያሉ:: ኮፍያዎቹ በማህበረሰቡ የዕደጥበብ ባለሙያዎች የሚዘጋጁ ናቸው:: የተለያየ አሰራር ያላቸው ሲሆን አሩዘ ከይሎታ/የሙሽራ ኮፍያ/፣ ነጪሕ ከሎይታ/ነጭ ኮፍያ/ እና ሌሎች ስያሜዎችንም የያዙ ናቸው:: አንዱን በጥልቅ የጥልፍ ጥበብ የተሰራ ኮፍያ ለመስራት ሳምንታት ወይም አንድ ወር ሊፈጅ ይችላል:: በተለይ የሙሽራ ኮፍያ ከሆነ በጥንቃቀዌ የሚሰራ በመሆኑ እስከ አራት ሺ ብር ድረስ ሊያወጣ ይችላል:: በዘርፉ የተሰማሩ የሐረሪ ሴቶችም ጥሩ ገቢ የሚያገኙበት የዕደጥበብ ውጤት ነው::
ከአለላ እና አልባሳት ወጣ ስንል ደግሞ የተለያዩ የእጅ እና የአንገት ጌጦችን በሐረሪ የዕደጥበብ ውጤቶች ውስጥ እናገኛለን:: አንደኛው ቀርማ የሚባው ሲሆን በግንባር ጫፍና በፀጉር መሐከል ላይ የሚደረግ ውብ ጌጥ ነው:: ጌጡ በተለያዩ ሐይማኖታዊ ባህላት፣ ባህላዊ ዝግጅቶች እና በሰርግ ወቅት ይደረጋል:: ቀርማ ከብር ማዕድን በቀጭኑ ተዘጋጅቶ በተለያዩ ገበያዎች ላይ ለሽያጭ ይቀርባል:: ሌላው ደግሞ በውበቱ እና ግርማ ሞገሱ ከሌሎች ጌጠች ከፍ ያለ ቦታ የሚሰጠው ወቅሪ የተባለው ጌጥ ነው:: ጌጡ በክብ ንብ ቀፎ አምሳያ የሚዘጋጅ ከብር የተሰራ የአንገት ላይ ማጌጫ በመሆን ያገለግላል:: አሰራሩ በአንድ በኩል የሚከፈት እና የሚዘጋ ሲሆን አንገት ላይ በሚያርፍበት ጊዜም በውስጡ የተለያዩ መኳኳያዎችን እና መሃረብንም ለመያዝ አመቺ ነው:: በመሆኑም ሴቶች በጭፈራ እና ጭብጨባ ወቅት በቀላሉ ከደረታቸው ላይ ወሰደው ውበታቸውን እንዲያገኙ ይረዳል:: ወቅሪ ከብር የተሰራ ጌጥ ቢሆንም የተለያዩ ተንጠልጣይ ዲዛይኖች የሚኖሩት በመሆኑ በግምት ከ150 ግራም በላይ የብር ማዕድን ሊፈጅ ይችላል:: ይህ ውድ የዕደ ጥበብ ውጤትም ታዲያ የሚዘጋጀው በጥበበኞቹ ሐረሪዎች ነው:: ተዝቆ ከማያልቀው የሐረሪዎች የዕደጥበብ ውጤቶች መካከል እነሆ የተወሰኑትን አቀረብንላችሁ እነጂ በርካታ ናቸው:: እኛም ይህን ጥበብ ወደ ሃብት በመቀየት የሴቶቹን አቅም ማሳደግ ይገባል እንላለን::
Ethiopian Harar peoples   


Ethiopia: በየመድሃኒት ቤቱ የሚቸበቸበው ትውልድ አደንዣዥ መድሃኒት


Domadol Addicted drug in Ethiopian Schools

ሱስ እንደፋሽን ተከታዩ በዝቷል:: ትውልድ እንደቀልድ ለሙከራ በጀመረው ስህተት አየተጠለፍ በሱስ ሰንሰለት ታስሮ መውጫ ቀዳዳ አጥቶ ይማስናል:: 
ከሲኤምሲ ወደ አያት እየተጓዘኩ ሳለሁ ከፊት ለፊቴ ያሉ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት መድሃኒታቸውን መግዛት እንዳለባቸው እያወሩ ነው:: አን ተማሪ 50 ብር ከቦርሳዋ አውጥታ ፊት ለፊቷ ከሚገኘው መድሃኒት መደብር ገባች። ከገዛችው መድኃኒት ውስጥ ለሶስቱም ጓደኞቿ አንድ አንድ አነስተኛ ካርቶን አከፋፈለቻቸው::
ሶስቱም ተማሪዎች በአንድነት ከካርቶኑ ያወጡትን አምፒሲሊን መሰል መድሃኒት የቻሉትን ያህን አራትም አምስትም ፍሬ ከማሸጊያው ላይ እየፈለቀቁ ወደአፋቸው ላኩት:: ከዚያ በኋላ ራሳቸውን መቆጣጠር እስኪሳናቸው ድረስ ተንገዳገዱ:: ሌሎች አልፎ ሂያጅ ተማሪዎች ግን እነርሱን እያዩ ይሳሳቃሉ:: መድሃኒቱን ለማወቅ ያለኝ ፈላጎት ጨመረ:: ወደመድሃኒት ቤቱ ሄጄ ሳጣራ ግን የህመም ማስታገሻ መድሃኒት ቢሆንም የማነቃቃት ባህሪ ያለውና ሱስ የሚያስይዝ እንክብል መሆኑንና ተማሪዎች በብዛት አንደሚጠቀሙት ተረዳሁ::
ከመድኃኒት ወሳጆቹ መካከል ሐያት / የተቀየረ/ ትገኝበታለች:: አዲስ አበባ ሲኤምሲ አካባቢ በሚገኘው ራህ ትምህርት ቤት የአስረኛ ክፍል ተማሪ ናት:: ዕድሜዋ በግምት 17 ሰባት ይሆናል:: በየቀኑ አዕምሮዋ አምጪ አምጪ የሚላትን መድሃኒት ካልወሰደች ድብርትና ድካም ይጫጫናታል፤ አዕምሮዋ ይረበሻል:: ምክንያቱም መድሃኒቱን በተደጋጋሚ በመውሰዷ ልክ እንደ ጫት እና ሲጋራ እሱን ካላገኘች እረፍት አይሰጣትም:: ቤተሰቦቿ ስለ ጉዳዩ ስለማያውቁ ሁሌም ደህና እደሆነች ነው የሚያስቡት:: እሷም ችግሯን ለመናገር አልደፈረችም።

ከመድኃኒቱጋር የተዋወቁት የዛሬ አራት ወር ገደማ እንደሆነ ትናገራለች። የትምህርት ቤት ጓደኛዋ ዶናዶል የሚባል መድሃኒት እዳለ እና እንደሚያነቃቃ ከሰማች በኋላ ለመሞከር ትወስናለች:: ወዲያውም መድሃኒቱን ገዝተው ጥቁር እና ቀይ ቀለማት የያዘውን እንክብል አምስት አምስቱን በአንድ ጊዜ ይውጡታል:: ሁለቱም ተዝለፍልፈው መውደቃቸውን ታስታውሳለች:: በትምህርት ቤቱ አካባቢ የነበሩ ወጣቶች በእጃቸው ላይ የነበረውን መድሃኒት ቀድሞም ስለሚያውቁት ደጋግፈው አንድ ጥግ ያሳርፏቸውና ምንም እዳልተፈጠረ የመጀመሪያችሁ ስለሆነ ነው አይዟችሁ በሚል አበረታተዋቸው ይሄዳሉ:: በዚህ የተጀመረው ሱስ አሁን ላይ በየቀኑ ሶስት እና አራት የትራማዶል/ዶናዶል/ እንክብሎችን እስከማስዋጥ እንዳደረሳት ትናገራለች::
በየቀኑም ከደብተር ቦርሳዋ ውስጥ በምትይዘው ትራማዶል የተሰኘውን መድሃኒት በትምህርት ቤት ምሳ ሰዓት ላይ ሶስት እንክብሎችን በአንዴ እንደምትውጥ ትናገራለች:: ማታም እዲሁ ከቤተሰቦቸ ተደብቃ ትደግመዋለች:: ይህ በየቀኑ የሚደረግ ልምድ ወደሱስነት እንደተቀየረ ብትረዳም ለመተው ተቸግራለች:: በየቀኑ ኬኒመውሰድ ሱስ ቢሆንባትም እስከ መቼ እንደዚህ ሆና እትቀጥል ግን ለእራሷም ግራ ገብቷታል:: አሁን አሁን ሱስ አስያዡን ካሻው መድሃኒት መደብር ሸምቶ በየቀኑ የሚቅመው ተማሪ ተበራክቷል:: እኔ ብቻ አይደለሁም አብዛኛው ተማሪዎች ይወስዱታል በማለት ችግሩ የእርሷ ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች እንደሆነ አስተውላላች:: በዚሁ መድሃኒት ባለፈው ወር ብቻ በአንድ ጊዜ አስር ተማሪዎች እራሳቸውን ስተው መውደቃቸውንም ትናገራለች:: መድሃኒቱ በ10 እና 15 ብር በየፋርማሲው ያለማዘየሚገኝ በመሆኑ የአራተኛ ክፍል ተማሪዎች ሳይቀሩ እይተጠቀሙት በመሆኑ አንድ መፍትሄ እንዲፈለግለት ትማፀናለች::
እኔም የሻጮቹ ጉዳይ እውነት መሆኑን ለማጣራት በአካባቢው ከሚገኘው ሊዲያ ወርቅነህ ወደ ተሰመድሃኒ መደብር አመራሁ:: ያለምንም የሐኪም ማስረጃ ይህንን ሱስ አስያዥ መድሃኒት በ15 ብር ከዝቼ ደረሰኝ ተቀበልኩ:: ከገዛሁ በኋላ ግን ፋርማሲስቷን እዴት ያለ ማለዣሸጭልኛለሽ ብላት መልሷ አንገ ማቀርቀር ብቻ ሆነ:: ጥፋት እንደሆነ ብታውቀውም ገንዘብ ነውና በየቀኑ ጠየቃት ሁሉ ትቸበችበዋለች:: ነገሩ ቢከነክነኝ ጉዳዩን ይዤ ወደ ተቆጣጣሪው ባለስልጣን አመራሁ::
ትራማዶል ወይም በአምራች ስሙ ዶናዶል የተባለው የመድሃኒት አይነት ሰውነት ውስጥ ከገባ በላ ወደ ሞርፊንነት የሚቀየር መድሃኒት መሆኑን የገለጹልኝ ደግሞ አዲስ አበባ የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ፋርማሲስት አቶ ይመር ሁሴን ናቸው:: እንደ እርሳቸው ገለፃ መድሃኒቱ ያለ የሐኪም ማስረጃ መሸጥ የሌለበት ቢሆንም በየመድሃኒት መደብሩ በግላጭ እንደሚቸበቸብ ይገልጻሉ::
መድሃኒቱ ሱስ ከማስያዙ በላይ ተማሪዎቹ ላይ የጉበት እና አደገኛ የመተንፈሻ አካላት በሽታ የማስከተል አቅም እንዳለው የሚናገሩት አቶ ይመር፤ሸጥ ካለበትም በሐኪም የታዘዘለት ታካሚ ብቻ ነው:: ነገር ግን ትክክለኛ አሰራር ተከትለው የሚሸጡ መደብሮች ቁጥራቸው ነስተኛ በመሆኑ በየቦታው እየተቸበቸበ ይገኛል:: ከሚታሰበው በላይ በርካታ ተማሪዎች እየወሰዱት ያለ መድሃኒትም ሆኗል:: መስሪያ ቤታቸው ተከታትሎ እርምጃ ለመውሰድ ያለው አቅም እና ክትትል ደካማ በመሆኑ በርካታ መድሃኒቶች ያለማዘዣ በመሸጥ ላይ መሆኑን ታዝበዋል:: በመሆኑም መድሃኒት መደብሮች ያለሐኪም ማስረጃ የትኛውንም አይነት መድሃኒት እዳይሸጡ ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚያስፈልግ አቶ ይመር ያሳስባሉ::
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ስለጉዳዩ ምንነት እና ስለሱስ አስያዡ መድሃኒት እና ስለተማሪዎች ግንኙነት ባለማቀወቃቸው መልስ ለመስጠትም አልተቻላቸውም:: ስነ አዕምሮ ህክምና ስፔሺያሊስት /ሳይኮሎጂስ/ አስመረት ወደብርሃን (/) እንደሚሉት፤ መድሃኒቱ ኦፖይድ የሚባል ሶስ አምጪ ንጥረ ነገር አለው። መድሃኒቱ የካንሰር ክመም፣ የመገጣጠሚያ በሽታ፣ ከቀዶ ጥገና በኋላ እና ለሌሎችም ህመም ሲያጋጥም ስቃይን ለመቀነስ ይረዳል። በአግባቡ ለህክምና ጥቅም ሲውል በአግባቡ ይሰራል። ነገር ግን ተማሪዎች በዘፈቀደ ሲወስዱት አካላዊ እና ሰነቦናዊ ጉዳት የማስከተል አቅም አለው። በመድሃኒቱ ምክንያት ሱስ ውስጥ የገቡ ወጣቶችም ልክ እነደማን'ውን የሱስ አየነት አስፈላጊው የስነአዕምሮ ህክምና ያስፈልጋቸዋል። ከሱሱ መላቀቅ ከፈለጉም የስነልቦና ሃኪሞች ጋር ቀርበው ተከታታይ ህክምና ማድረግ ይገባቸዋል። መድሃኒቱን በማቋርጥበት ወቅት ምን ችግር ይደርስብኛል ብለው ለሚሰጉም በሚሰጠው ህክምና አማካኝነት ከችግሩ የሚያላቅቁ አጋበጊዜያቶች ሂደት ከሱሱ ለመላቀቅ የሚያግዙ መድሃኒቶችንም ያገኛሉ። ለአብነት ዶናዶልን ሲያቋርጡ እንቅልፈ እጦት ካጋጠማቸው በምትኩ የእንቅልፍ መድሃኒት፤ ድብርት ካጋጠማቸው ደግሞ ዘና የሚያደርጉ ጤነኛ መንገዶችን ለአማራጭነት ከሃኪሞች ማግኘት ይችላሉ። በመሆኑም የሱስ ተመራጭ የለውምና ተማሪዎቹ ላይ የሚታየውን ችግር ተረባርቦ መቅረፍ ለአገርም ይበጃል።

Featured post

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

                    የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደር...