Sunday, April 5, 2020

ከእኛ የተረፈውን መብላት ሲገባት ከእርሷ የተረፈውን እንበላለን


የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ ብልህ እና አርቆ አሳቢ ነው። ከጥንት የጋርዮሽ ዘመን ጀምሮ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ሲጠቀም ኖሯል። በቤቱ ውስጥም እንስሳትን እያላመደ ያቆያል። ነገር ግን አንድ ለማዳ ሳትሆን በቤቱ ውስጥ የምትራመስ ጎጆዋን በሰው ጎጆ ቀልሳ የምትኖር እንስሳን ጨርሶ ማራቅ አልቻለም። ብዙዎች ስሟን እንኳን ለመጥራትን ሲቀፋቸው ይስተዋላል። አይጥ በእንግሊዘኛው አጠራር mouse ወይም rat አፈጣጠሯ ከአጥቢ እንስሳት መካከል ትመደባለች። እንዲሁም በፈጣን እንቅስቃሴዋ እና በማሽተት ችሎታዋ ከፍተኛነት ትታወቃለች።
የአይጥ እድሜ 18 ወራት ሲሆን፤ በርካታዎቹ ግን በተለየዩ አደጋዎች ምክንያት አንድ አመት ሳይሞላቸው ይሞታሉ። በአብዛኛው በእንጨት እና ከአፈር በተሰሩ ቤቶች ውስጥ በቀላሉ ገብታ ለመኖር የሚያስችላል ጠንካራ ጥርሰንም ታድላለች። አንዳንዴም በድንጋይ እና በብሎኬት በተሰሩ ቤቶች ውስጥ ከገባች ዘሮቿን በማብዛት ተደላድላ ለመኖር አትቸገርም። እናም በኢትዮጵያ ደግሞ አብዛኛው ቤቶች የተሰሩት ከአፈር እና ከእንጨት በመሆኑ በእያንዳዱ ጓዳ ውስጥ አለች ቢባል ማጋነን አይሆንም። አለቃ ገብረሃናም ምግብ በሚበሉበት ቤት ውስጥ ትንሿ እንስሳን ከእንጀራ ማስቀመጫው ስፍራ በማየታቸው ከሞሰቡ አይጡ ብለው መቀኘታቸውን ታሪክ ይነግረናል። ነገሩ ጥንትም ትንሿ እንስሳ እንደ ድመት ከሰዎች ጋር ተላምዳ ቤት ውስጥ እንትኖር አይፈቀድላት እንጂ በእያንዳንዱ ቤት ግን በየስርቻው የመገኘቷን ጉዳይ ያሳያል። ያለፈቃድ በቤት ውስጥ የመገኘቷ ጉዳይም ብዙዎችን ሲያንገበግባቸው ይኖራል።
በተለይ የሰፈራችን እድሜ ጠገብ ልብስ ሰፊ አቶ አክሊሉ እንስሳዋን ክፉኛ አይወዷትም። በአንድ ወቅት በቤታቸው ራዲዮናቸውን ከፍተው አረፍ በአሉበት ያለአንዳች ምክንያት ከዘራቸው ላይ ተጠምጥማ ስታበቃ ወደ ጉድጓዷ የገባችበት ጊዜ ለእርሳቸው እንደ ህልም ነው። ከዚያ ጊዜ ወዲህ ላገኙት ሰው ሁሉ ይቺ ከይሲ ፍጥረት ከዘራዬን አረከሰችው እያሉ ለለቅሶ እና ለጥየቃ በየሄዱባቸው በቦታዎች ሁሉ ሲያንቋሽሿት ይውላሉ። አጥይ ብለው እንኳን ደፍረው መጥራት ስለማይሆንላቸው «ስሟን ቄስ ይጥራውና» እያሉ ነው ወጋቸውን የሚጠርቁት። እናም በየዕለቱ ወጥመድ ቢያዘጋጁ፤ መርዝ ቢነሰንሱ መንታ የመሰሉ ዝርያዎቿን ይገድላሉ እንጂ ጭራሽ ልትጠፋ አልቻለችም። አይጥ አዳኝ የተባሉ ድመቶችን በቤታቸው ውስጥ ቢያሰማሩም ድመቶቹ ከመንደሩ በሚቃርሙት ትርፍራፊ ምክንያት ሆዳቸውን እየነረቱ የቤቱ አሮጌ ሶፋው ላይ መገላበጡት ተያይዘውታል። በመሆኑም እንስሳዋን ከቤታቸው ለማጥፋት አዲስ መላ በአዕምሯቸው እስኪመጣላቸው ድረስ እንደተናደዱ ይኖራሉ።
አንድ ቀን ታዲያ አዛውንቱ ከስራ ወደ ቤታቸው ገብተው አረፍ እንዳሉ ባለቤታቸው ምግብ ለማቅረብ ሞሰቡን ከፈት ቢያደርጉት አጅሪት ተስፈንጥራ ወጥታ በአልጋቸው ስርቻ ውስጥ ተደበቀች። አቶ አክሊሉም የዛን ቀን እህል አልበላም ብለው እስክ ምሽቱ ሶስት ሰዓት ድረስ ሲገላገሉ ቆይተው ደረቅ ዳቦ አስገዝተው ተመገቡ። አቶ አክሊሉ ነገሩ የከነከናቸው እርሳቸው ያልበሉትን እንጀራ እንዴት አይጧ ቀድማ ትመገበዋለች የሚለው መበለጥ ነበር። ባለቤታቸው ደግሞ «የዛሬን ነው እንዴ አይጧ ሁሌስ ሽር የምትለው ከሞሰቡም አይደል እንዴ» ብለው ንዴታቸውን የሚያባብስ ንግግር አከሉላቸው። «እንዴት በተከበርኩበት አገር አንዲት መናኛ ጅራታም እንስሳ ለፍቼ ያገኘሁትን ምግብ ቁጭ ብላ ትሰለቃለች» በሚል እልህ እንስሳዋን ለግድያ ሲፈልጓት አደሩ። ቤቱን አመሰቃቅለው ያገኙት ግን በሶስት ክፍል ቤታቸው ውስጥ የሚገኙ አስር ጉድጓዶችን ብቻ ነበር። አስር ጉድጓዶች ስትፈለፍል እኔ የት ነበርኩ ብለው እራሳቸውን ቢጠይቁም መልስ አላገኙም። ምክንያቱም አንድም ቀን ከቤታቸው ውጪ አድረው አያውቁም ነበር። ከተማሰው ቤታቸው ይልቅ ግን የአባወራነታቸው ቀድሞ የመመገብ ክብር መደፈሩ አልዋጥ ብሏቸዋል።
አዛውንቱ ሚስት ከአገቡ ወዲህ ዶሮ ወጥም ይሰራ፣ እንጀራም ይጋገር ምንአለፋችሁ ማንኛውም ምግብ ከተሰራ ቀደሞ የሚቀርበው ለእርሳቸው ነበር። አሁን ግን ስሟን እንኳን በወጉ በማይጠሯን እንስሳ ተቀድመዋል። ለአቶ አክሊሉ ከአይጧ ጋር የያዙት እልህ አስጨራሽ ትግል ቀድሞ የመብላት እና ያለመብላት ነው። በመሆኑም ጉዳዩ ለእርሳቸው የሞት እና የሽረት ያክል ሆኗል። ነገን አግኝቿት ልኳን ካሳየኋት በኋላ አባወራነቴን አስከብራለሁ በሚል ሃሳብ ሌት ተቀን እንስሳዋን የሚያጠፉበት መንገድ እንዳሰላሰሉ ናቸው። እርሷም ቀድማ ምግቡን መቀማመሷን አላቆመችም።
እናም አማካሪም ሆነ ሁነኛ ባለሙያ ሲያፈላልጉ ሰባት የሰቆቃ አመታትን ያሳለፉት አዛውንት ያለፈው እሁድ እለት ልባቸው እንደተረጋጋ የሰማ ጎረቤት ሁሉ ቤታቸውን ከአፍ እስከ ገደፉ አጥለቅልቆት ሰንብቷል። ላገኙት ሰው ሁሉ ይችን እርኩስ መና የሚያስቀር ቴክኖሎጂ አጊኝቻለሁ እያሉ ይናገራሉ። ቀድመው በቤታቸው ለመመገብ የሚያስችላቸውን እድል የተነፈጉ አባወራዎች ሁሉ የቴክኖሎጂው ተቋዳሽ ለመሆን ጓጉተዋል። አቶ አክሊሉ ግን መፍትሄውን በቤታቸው ከሚያስነግሩ ይልቅ በእድር ጡሩንባ ወይም በራዲዮን ቢያስነግሩ ነበር አንጀታቸው የሚርሰው።
ነገር ግን የሰፈሩ ሰው ጉትጎታ ስላላፈናፈናቸው ይፋ ለማድረግ ከተሰብሳቢው መካከል እንደተወካይ የሚያገለግሉ አራት ሰዎች መርጠው መደ ቤታቸው ጓደ ይዘዋቸው ገቡ። ኩራት በተላበሰ አነጋገር «ይህ የምትመለከቱት ከብረት የተሰራ መሶብ አንድም እንስሳ የማያስገባ ከመሆኑም በላይ ቁልፉ በባለቤቴ እጅ ላይ ብቻ ይገኛል። ሲፈለግ በኩልፍ ይከፈታል ሳይፈለግ ደግሞ ይዘጋል። በመሆኑም ያች እርኩስ እንስሳ ከእኔ የተረፈውን ወዳድቆ ታገኝ የሆን እንጂ ቀድሞ የመብላቷ ጉዳይ አበቃለት» ብለው በክብ ቅርጽ የተሰራውን መሶብ እንደተዘጋ አሳዩ። አራቱ አባወራዎች አዲሱን ግኝት በአድናቆት ከተመለከቱ በኋላ ሳሎን ለተሰበሰበው ሰው ለማስረዳት በሽግድምድሞሽ እርምጃ ቀኝ ኋላቸውን ያዙ። ለተብሳቢውም አዲሱ ግኝት በሰበዝ ከሚሰራው መሶብ ይልቅ የተሻለና አይጥም ሆነ በረሮ ሊያሳልፍ እንደማይችል አጠናክረው የአይን እማኝነታቸውን በየተራ አቀነባብረው አሰሙ። 
GT
አባ አክሊሉ እና ቀድሜ እንድበላ
 
ከወደ መስኮቱ ስር የተሰበቡት ወይዛዝርቶች ግን አዲሱ ግኝት ላይ ፊታቸውን እነደማዞር አደረጉበት። የብረት ሞሰቡ ሙቀት ሲነካው እንጀራውን በፍጥነት የማሻገት እድሉ ሰፊ ስለሚሆን ምግቡን በየቀኑ ማሞቅ እነደሚኖርባቸውና ለተጨማሪ ስራ እንደሚዳርጋቸው ቅሬታ በማንሳት ማጉረምረም ጀመሩ። አቶ አክሊሉ በዚህ ጊዜ ግኝታቸው እንዳይዋደቅባቸው በመስጋት በፍጥነት ተነስተው በከፍተኛ ድምጽ ምግቡ እንዳይበላሽ ካስፈለገ ወደ ፊት የብረቱ መሶብ ማቀዝቀዣ ያለው እንዲሆን ከባለሙያዎች ጋር መነጋገር እንደሚቻል ተናገሩ። ለአሁኑ ግን ለአንገብጋቢው ችግሩ መፍትሄ መገኘቱን በማብሰር ጉዳዩን በአጭሩ ደመደሙት። መሶቡንም «ቀድሜ እንድበላ» የሚል ስም ካወጡለት በኋላ ሁሉም በየቤቱ ቢጠቀምበት አይነተኛ ዘዴ መሆኑን በመንደሩ ነዋሪ ፊት ማስታወቂያ ሰሩለት።
«ቀድሜ እንድበላ» የተሰኘው መሶብ በአቶ አክሊሉ ቤት ግልጋሎት ላይ እየዋለ ቢሆንም በተቀሩት የመንደሩ ሰዎች ቤት ግን ጥቅም ላይ ለማዋል የአዛውንቱ ባለቤት ተሞክሮ መረጋገጥ ስለነበረበት ጥቂት ቀናት ለመጠበቅ የግድ ሆኖ ነበር። የአቶ አክሊሉ ባለቤት ግን ሩህሩህ እና አይጥም እንስሳ ነው ምን በልቶ ያድራል የሚል አስተሳሰብ የያዙ በመሆናቸው የቀድሜ እንድበላን ጥቅም በሙሉ ልባቸው ወደ መንደሩ ለማስተላለፍ አልቻሉም። ደግሞም ሁል ጊዜ መሶብ እየቆለፉ እና እየከፈቱ ምግብ ማውጣት እና ማስገባት አሰልቺ መሆኑን በመረዳታቸው እስከዛሬ የኖርኩበት ነው ያገኘሁትን በመሶብ አስቀምጬ ብበላ ይሻለኛል የሚል ሃሳብ እንዳደረባቸው መገመት አያስቸግርም። እናም የአዲሱ ግኝት ጥቅም በወይዘሮዋ ማረጋገጫ ማጣት እና በአንዳንድ ቸልተኛ አባወራዎች ቀድሞ የመብላት ፍላጎት ማነስ ምክንያት ሳይስፋፋ ቀረ። አቶ አክሊሉ ግን ባለቤታቸው ላይ ባሳደሩት ጫና ምክንያት ከሚጠሏት እንስሳ በፊት በቤታቸው ቀድሞ የመብላትን ደስታ በየቀኑ ማጣጣማቸውን ቀጥለዋል። እውነት ግን እንደ አዛውንቱ ከእኛ የተረፈውን መብላት ሲገባት ከእርሷ የተረፈውን መብላታችን የሚያስቆጨን ስንቶቻችን እንሆን።

Friday, October 11, 2019

Dr. Abiy Ahmed win - Nobel Peace Prize

Abiy Ahmed Awarded Nobel Peace Prize

Mr. Abiy, the prime minister of Ethiopia, spearheaded a peace accord in his region and catalyzed reforms at home.
Abiy Ahmed, the prime minister of Ethiopia, was awarded the Nobel Peace Prize on Friday, for his work in restarting peace talks with neighboring Eritrea, ending a long stalemate between the two countries. 
 Dr Abiy Ahmed prime minister of Ethiopia
Mr. Abiy, 43, broke through two decades of frozen conflict between his vast country, Africa’s second most populous, and Eritrea, its small and isolated neighbor.
The two nations share deep ethnic and cultural ties, but until July last year they had been locked into a state of neither peace nor war, a conflict that had separated families, complicated geopolitics and cost the lives of more than 80,000 people during two years of border violence.
Ethiopia and Eritrea share deep ethnic and cultural ties, but until July last year they had been locked into a state of neither peace nor war, a conflict that had separated families, complicated geopolitics and cost the lives of more than 80,000 people during two years of border violence.
The peace accord signed more than a year ago between Mr. Abiy and President Isaias Afwerki of Eritrea has only slowly translated into concrete steps to reconnect the two nations.
But it has been held up as an example of how historic change can come about in even the oldest and most intractable conflicts. Diplomatic relations between Ethiopia and Eritrea have resumed, and the two leaders and senior officials from the two nations have met frequently to discuss how to reconnect their nations.
Importantly, telecommunications have been restored, allowing families that were split up in the war to contact each other. In the days that followed this breakthrough, some Ethiopians called Eritrean numbers randomly, and vice versa, just to speak to someone on the other side, simply because they could. Others tracked down parents, siblings and friends.
When the first commercial Ethiopian Airlines flight from Addis Ababa to the Eritrean capital, Asmara, landed on July 18 last year, passengers stepping off the plane fell to their knees and kissed the ground. Two sisters separated from their father in the war, stuck on opposite sides of the border, embraced him for the first time after 20 years of growing up with him.
Nadia Murad and Denis Mukwege jointly won the award in 2018. Ms. Murad, 26, a Yazidi woman, became the voice and face of those who survived sexual violence at the hands of Islamic State militants. Dr. Mukwege, 64, is a Congolese gynecological surgeon who has treated thousands of women in his war torn home country.
  • The prize for medicine and physiology was awarded to William G. Kaelin Jr., Peter J. Ratcliffe and Gregg L. Semenza for their work in discovering how cells sense and adapt to oxygen availability.
  • The prize for physics was awarded to James Peebles, Michel Mayor and Didier Queloz for their contributions to the understanding of the evolution of the universe and the Earth’s place in the cosmos.
  • The prize for chemistry was given to three scientists — John B. Goodenough, M. Stanley Whittingham and Akira Yoshino — who developed lithium-ion batteries, the energy storage systems that have revolutionized portable electronics.
  • The 2018 and 2019 Nobel Prizes in Literature were both awarded this week to Olga Tokarczuk, a Polish author, and Peter Handke, an Austrian writer. Last year’s prize was postponed after the husband of an academy member was accused, and ultimately convicted, of rape. That crisis that led to the departure of several board members and required the intervention of the King of Sweden.
Source- Netyork times

Friday, October 4, 2019

ዋሻ አምባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም


ከአዲስ አበባ ወደ ባሕር ዳር የሚወስደውን የአስፋልት መንገድ ይዘው ሲጓዙ ፍቼ፣ ደብረ ጉራቻ፣ጎሀ ጽዮን ከተሞችን አልፈው የዓባይን በረሃ ካጠናቀቁ በኋላ የደጀን ከተማን ያገኛሉ፡፡ ጉዞዎን በመቀጠል ...
የምሥራቅ ጎጃም ዋና ከተማ ደብረ ማርቆስን እንዳለፉ አማኑኤል ከተማ ይደርሳሉ፡፡ የአማኑኤል ከተማ ከአዲስ አበባ 330 . ርቀት ላይ የምትገኝ የማቻክል ወረዳ ዋና ከተማ ናት፡፡ ከአማኑኤል ከተማ ወደ ግራ ታጥፈው በጠጠራማው መንገድ ዐሥር ኪሎ ሜትር ያህል ከተጓዙ በኋላ አማሬ የምትባል አነስተኛ የገጠር መንደር ያገኛሉ፡፡

ትንሽ እንደተጓዙም ግራራም ማርያም ቀበሌ ይደርሳሉ፡፡ በዚህ ቀበሌ ውስጥ በርካታ ተፈጥሮአዊ ጸጋዎች ይገኛሉ፡፡ በደን የተሸፈኑ ተራሮችን በመካከላቸውም ድንቅ ሸለቆ ፈጥሮ የሚያልፈው ‹‹የሸማ ማጠቢያ›› ወንዝ ይገኛል፡፡ ወንዙ ከፀሐይ መግቢያ ወደ ፀሐይ መውጫ ቁልቁል ሲፈስ ላየው ተፈጥሯዊ ውበቱ ይማርካል፡፡ የሸማ ማጠቢያ ወንዝ ከተፈጥሯዊ ውበቱ ባሻገር ለአካባቢው አርሶ አደሮች የፍራፍሬና አትክልት ልማት አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

ጥቂት እንደተጓዙ ድንገት የሚታይ የቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ይደርሳሉ፡፡ ከቅዱስ ዑራኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በግራ በኩል ደግሞ የዋሻ አምባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳምን የእንስሳት ማደሪያ የሆነውን ቆርቆሮ ቤት ያያሉ፡፡ የከብቶችን ቤት ወደ ግራ እየተው ደረጃውን ቁልቁል መንገድ ይዘው ሲጓዙ ቀጭን መንገድ ያገኛሉ፡፡

ከዚያም በቆርቆሮ ክዳን የተሠራውን የተግባር ቤት የገዳሙ ምዕመናን ምግብ የሚዘጋጅበትና የሚታደልበት ቤት ነው፡፡ በዚህ ቤት ውስጥ መቀነታቸውን ታጥቀው፣ ቆባቸውን ደፍተው፣ እንጀራ የሚጋግሩ፣ ወጥ የሚሠሩ፣ ማገዶ የሚያቀርቡ እንስት ባሕታውያን በየዕለቱ በትጋት ሲሠሩ ይመለከታሉ፡፡
 
 እማሆይ ወለተ ማርያም




ከተግባር ቤቱ ወደ ፀሐይ መግቢያ ታጥፈው የአቀበቱን ጉዞ መያያዝ ግድ ይልዎታል፡፡ በዚህ መንገድ ላይ ሲጓዙም በግራ ቀኝ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን ያገኛሉ፡፡ ወደፊት ጥቂት እንደተጓዙም የተለያዩ ምንጮች ከከፍታ ቦታ በስተቀኝ በኩል ሁለት ሰፋፊ ዋሻዎችን ያያሉ፡፡ የመጀመሪያው ዋሻ ወደ ገዳሙ የሚመጡ ጠበልተኞች የሚያርፉበትና ምግባቸውን የሚያበስሉበት ትልቁ ዋሻ ነው፡፡ በዚህ የዋሻ በር የቀኝ ጠርዝ ላይ ከምድር እስከ ዋሻ ጣራ ድረስ በድንጋይ ካብ የተሠራና ጠንካራ የጣውላ መዝጊያ የተገጠመላት ትንሽ ቤት ያያሉ፡፡ ይህች አነስተኛ ቤት የገዳሙ መሥራች ቤት ናት፡፡
የገዳሙ መግቢያ

ትልቁንም ዋሻ በቀኝ በመተው፤ ወደ ግራ ደግሞ ገደላማውን ቦታ እየቃኙ ወደፊት ጥቂት እንደተራመዱ ሁለተኛውን ዋሻ ያገኛሉ፡፡ ይህ ዋሻ ከመጀመሪያው ዋሻ ጋር በተፈጥሮ ግድግዳ ተያይዟል፡፡ በዚህ ዋሻ ፊት ለፊት ደግሞ ከከፍታ ቦታ እየተወረወሩ ወደ ገደሉ የሚወርዱ ሦስት ትንንሽ ጅረቶችን ያገኛሉ፡፡ አንደኛውን ፏፏቴ እልፍ እንዳሉም የዋሻ አምባ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳምን ያገኛሉ፡፡ ይህ ገዳም ሁለት በሮች አሉት፡፡

በመጀመሪያ ከውጪ ወደ ዋናው የሚገባ ሰው ምንም ነገር ማየት አይችልም፡፡ ለዓይን የማይታይበት ድቅድቅ ጨለማ ነው የሚያጋጥመው፡፡ ድቅድቁ ጨለማ ቀስ በቀስ እየተገፈፈና ዓይን ጨለማውን እየተለማመደ ሲሔድ የዋሻውን ምዕራባዊ ዳርቻ ይመለከታሉ፡፡ ዋሻው ከምዕራብ ወይም ከፀሐይ መግቢያ ወደ ምሥራቅ ወይም ፀሐይ መውጫ በቁመት ከፍ እያለ ይሔድና ከበሮቹ ላይ በሚገናኝበት ቦታ ላይ ከሁለት ሜትር ርቀት የበለጠ ቁመት አለው፡፡
ከምስራቅ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ወደ ዋሻ ሲገባ ያለው የጣራ ርዝማኔ እየቀነሰ ይሔድና ከተፈጥሮ የድንጋይ ግድግዳ ጋር ይዋቀራል፡፡ ሰፊው የዋሻ ክፍል የቅዳሴ አገልግሎት የሚሰጥበት ሲሆን በዋሻው የግራ ጠርዝ መጨረሻ ላይ ያለው ደግሞ የተለያዩ ጽላቶች የሚገኙበት ቤተ መቅደስ ነው፡፡ ያላየናቸው ዋሻዎችና ሌሎች ምሥጢራዊ ሀብቶችን ባለቤቱ ያውቀዋል፡፡ ቅዱሳን ያውቁታል፡፡ እማሆይም ሊያውቁት ይችላሉ፡፡

ከዋሻው በር በውጭ የቀኝ አቅጣጫ በአናት በኩል ሁለት ጅረቶች ከከፍታ ቦታ ወደ ታች እየተወረወሩ ፊት ለፊት ካለው ገደል የመዋኛ ገንዳ ከሚመስለው ይቀላቀላሉ፡፡ አንደኛው የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ጠበል ሲሆን፤ ከዚያ እልፍ ብሎ ደግሞ ከአንድ ምሰሶ ሥር የሚፈልቅ የቅዱስ ዑራኤል ጠበል ይገኛል፡፡

ከመጀመሪያው ዋሻ ወደ ገዳሙ ዋሻ ሲኬድ በሁለተኛ መስመር ላይ ከሚገኘው አነስተኛ ምንጭ ሥር አንድ ዛፍ ከዚህ ውሃ እየተመገበ ሥር ሰዶ ድንጋዮችን ሰንጥቆ ገብቶ አድጎ ይታያል፡፡ ይህ እንጨት ከድንጋይ በላይ ያለው አካሉ የመስቀል ቅርፅ ያለው ነው፡፡
የዋሻ አምባ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም በአማራ ብሔራዊ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን ማቻክል ወረዳ ግራራም ቀበሌ የወንዶችና የሴቶች ገዳም ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡

ገዳሙ እንዴት ተመሠረተ? በማንስ ተመሠረተ?

ወይዘሮ ድንቃየሁ ከዋሻ አምባ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም በአጭር ርቀት ላይ በሚገኘውና ቂርቆስ በተባለው የገጠር ቀበሌ ከአርሶ አደር ቤተሰብ ውስጥ ነው የተወለዱት፡፡ ለዘመናዊም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን ትምህርት አልታደሉም፡፡ ዕድሜአቸው ለቅመ ሔዋን ሲደርስ ወላጆቻቸው በአካባቢው ባሕልና ወግ መሠረት ዳሩአቸው፡፡ ከዚያም ወይዘሮ ድንቃየሁ ቤት ሠርተው ጎመን ዘርተው የሞቀ ትዳር ባለቤት ሆኑ፡፡ ሁለት ልጆችንም አፈሩ፡፡ በዚህ የትዳር ሕይወታቸው ላይ እያሉ በተደጋጋሚ በሕልም ይታያቸው ነበር፡፡

ወሩን ቀኑንና ዓመተ ምሕረቱን ለይተው በማያውቁት አንድ ሌሊት በርካታ ካህናትና ቀሳውስት በተሰበሰቡበት ቦታ ላይ ይደርሳሉ፡፡ ከእነዚህ ሰዎች መካከል ከፊሎቹ ቀዮች ከፊሎቹ ደግሞ ጥቁሮች ነበሩ፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁ በእነዚህ ሰዎች መካከል ለመቀመጥ ሲሞክሩ አንድ ክንፍ ያለው ቀይ ሰው እጃቸውን ይዞ እየመራ ከዋክብት ወዳሉበት አንድ ቦታ ያደርሳቸዋል፡፡

 ከዚያም ይህ ሰው ከመሬት ወደ ሰማይ የተዘረጋ ቀጭን የብረት መሰላል እያሳየ በዚያ መሰላል ላይ ወደ ላይ እንዲወጡ ይነግራቸዋል፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁ እንደታዘዙት መሰላሉን እየፈሩ እየቸሩ ወደ ላይ መውጣት ይጀምራሉ፡፡ የመሰላሉን ግማሽ ያህል እንደወጡ ወደታች ሲመለከቱ ጥቋቁር ሰዎች ያሉበትን ገደላማ መሬት ያያሉ፡፡ በዚህ ጊዜ በመንታ ሃሳብ ውስጥ ሆነው ቆም ብለው ወደላይ ለመቀጠል እንዳልቻሉ ሲያስቡ ወደታች ለመመለስ በመሬት ላይ ሆነው የሚጠባበቋቸው ጥቋቁር ሰዎች ጉዳት እንደሚያደርሱባቸውና ገደል እንደሚገቡ እየተጨነቁ እያሉ ያው እየመራ ያወጣቸው ሰው ‹‹ቀጥይ አትፍሪ›› በሚል ያበረታታቸዋል፡፡

 ወይዘሮ ድንቃየሁ የጀመሩትን የመሰላል መውጣት ትግል ቀጥለው መጨረሻ ላይ አራት ዙር አጥር የመሰለ ነገር ላይ ያርፋሉ፡፡ በዚያ ቦታ ቤተ መንግሥት አለ፡፡ በእያንዳንዱ አጥር በር ላይ ዘበኞች ቆመዋል፡፡ የመጀመሪያው ዘበኛ ወደ ሁለተኛ የሁለተኛው ወደ ሦስተኛ የሦስተኛው ወደ አራተኛ ዘበኛ በር እየከፈቱላቸው መንገድ እየመሩ ካስተላለፏቸው በኋላ መጀመሪያ መሰላሉን እንዲወጡ ያዘዛቸው ቀይ ሰው ወደ ከበሮ መሰል ቤት ያስገባቸውና ‹‹አይዞሽ አትፍሪ፤ ከእንግዲህ የሚያገኝሽ የለም በቃ›› የሚል ማጽናኛ ቃል ይነግራቸዋል፡፡ ወዲያው ከእንቅልፋቸው ይነቃሉ፡፡ምን ይሆን እያልኩ አደንቃለሁ እፈራም ነበርአሉ እማሆይ፡፡

 ሌላ ጊዜ ደግሞ ትዳራቸውን ትተው ለመውጣት ምክንያት የሆናቸውን ሕልም አዩ ሀገር በእሳት ሲለበለብና ሕዝቡ ሁሉ ከዚህ እሳት ለማምልጥ ሲሮጥ ይመለከታሉ፡፡ እሳቸውም ከእሳቱ ሮጠው አምልጠው ሲሄዱ በተደጋጋሚ ያያሉ፡፡ይህ የእግዚአብሔር ጥሪ ነው፡፡ብለው ሀብት ንብረቴን፤ ልጆቼን ሳይሉ ትዳራቸውን ትተው ወደ ወላጆቻቸው ቤት ይመለሳሉ፡፡ የፈጣሪያቸውን መንገድ መርጠውና ፈቅደው የመንፈሳዊ ሕይወት ጉዞአቸውን ለመጀመር ጎጇቸውን ተሰናበቱ፡፡

 ወይዘሮ ድንቃየሁ ወደ ወላጆቻቸው ቤት እንደተመለሱ ቀን ቀን አብዛኛውን ጊዜአቸውን ወደ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ በማስቀደስና ስብከተ ወንጌልን በማዳመጥ ማሳለፍ የዕለት ተዕለት ተግባራቸው አደረጉት፡፡ ድንገት ተነስተው ግን ወደ ሌላ ቦታ ተጓዙ፡፡ ቦታው አሁን ካለበት በግምት 65 ኪሎ ሜትር በላይ በሚርቀውና ‹‹ሰሳ ገዳም›› እየተባለ በሚጠራ ቦታ ነው፡፡ ሰሳ ገዳም ከደረሱ በኋላም ለሰባት ወር በዚያም ተቀመጡ፡፡ ሰሳ ገዳም ከደብረ ማርቆስ ከተማ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ አባ አስራት ገዳም ከሚባለው ጥንታዊ ገዳም አካባቢ የሚገኝ ገዳም ነው፡፡ ከሰባት ወር የገዳም ቆይታቸው በኋላም እንደገና ወደ ወላጆቻቸው ቤት ተመለሱ፡፡

 ወደ ወላጆቻቸው ቤት እንደተመለሱም እንደተለመደው ወደ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን እየተመላለሱ ማስቀደስና በዚያው ጸሎት ሲያደርሱ መዋል የዕለት ከዕለት ሕይወታቸው ሆነ፡፡ ይህ በእንዲህ ታላቅ እኅታቸውሰኔ ጎልጎታ መጸሐፍ ገዝተሸ አንብቢብላቸው ስለነበር እንዳለ አንድ ቀን እናታቸው ወደ ከተማ ለገበያ ለመሔድ ሲዘጋጁ መጽሐፍ እንዲገዙላቸው ይጠይቃሉ፡፡ እናትም ‹‹አንቺ አልተማርሽ፤ ፊደል አትለዪ መጽሐፍ ምን ያደርግልሻል?›› ብለው ይመልሱላቸዋል፡፡

ወይዘሮ ድንቃየሁም ግድየለም መጽሐፉን ባየው ብሳለመውስ? የሚል መልስ ይሰጧቸውና እናት ወደ ገበያ ሊወጡ ሲሉ የምትገዢልኝ ደግሞ የሰኔ ጎለጎታ መጽሐፍን ነው ብለዋቸው ይለያያሉ፡፡ እናትም የሰኔ ጎለጎታን መጽሐፍ ከገበያ አጠያይቀውና ገዝተው ያመጡላቸዋል፡፡ መጽሐፉን እየገለጡ ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላድንግል ሆይ ምንም እንኳን እንደምኞቴ ጸሎትሽን ማንበብና መድገም ባልችልም ጸሎትሽን እንደጸለይኩ አድርገሽ ቁጠሪልኝ፡፡እያሉ በመማጸን መጽሐፉን ይዘጋሉ፡፡

 ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ተአምር ይከሰታል፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁ እናታቸው የገዙላቸውን የሰኔ ጎልጎታ የቅድሰት ድንግል ማርያም የጸሎት መጽሐፍ እየገለጡ ገጽ በገጽ እያገላበጡ ሲመለከቱ ይቆዩና አጥፈው መማጸናቸውን ይቀጥላሉ፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁ ሳያስቡት የሰኔ ጎልጎታን ከገጽ እስከ ገጽ ማንበብ ጀመሩ፡፡ ይህን የሰሙ እናታቸውምዛሬ ደግሞ ከማን ጋር ታወሪያለሽሲሉ ይጠይቋቸዋል፡፡ 

እዪው መጽሐፉን ማንበብ ቻልኩ እኮ፡፡ ስሚበማለት የንባብ ችሎታቸውን ያሰሟቸዋል፡፡ እናትም በነገሩ ተደንቀው ልጃቸውን ወይዘሮ ድንቃየሁን ወደ ንስሐ አባታቸው ይዘው ይሔዳሉ፡፡ የንስሐ አባታቸውን በቤተ ክርስቲያን ያገኙና የሆነውን ሁሉ ይነግሯቸዋል፡፡ ቄሱ ነገሩን ማመን ቢሳናቸውም የተባለውን ድንቅ ተአምር ለመስማት መርጠው ወይዘሮ ድንቃየሁ መጽሐፉን በንባብ እንዲያሰሟቸው ጠየቋቸው፡፡

 መጽሐፉን ቃል በቃል እያሰሙ ገጾችን እያገላበጡ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው አነበቡ፡፡ ቄሱም እየተደነቁና እየተገረሙ ሁሉንም ካዳመጡ በኋላ ‹‹እግዚአብሔር የጀመረልሽን ፀጋ ከዳር ያድርስልሽ፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም አትለይሽ፡፡ ያነበብሽው ጸሎት ድንግል ማርያም በአማልጅነቷ ለአማኞች ያቀረበችው ጸሎት ነው፡፡ 

 በስሟ መጽሐፍ ለጻፉ፣ ቤተ ክርስቲያን ለሠሩ፣ በስሟ ምጽዋት ለመጸወቱ፣ ለቤተ ክርስቲያን ዕጣን፣ ጧፍ ላበረከቱ ምሕረት ጸጋ ይሰጥ ዘንድ ለልጇ ለኢየሱስ ክርስቶስ በመቃብሩ በጎልጎታ ላይ ሆና ያቀረበችለት ልመና ነው፡፡ ልጇም እናቱ የጠየቀችውን ሁሉ ለመፈጸም ቃል ገብቶላታል፡፡ በቃለ መሃላም አረጋግጦላታል፡፡ ይህን ነው አሁን ያነበብሽው፡፡ ጸሎትና ክርስቶስም ለእናቱ የገባውን ቃል ኪዳን ለአንችም ይፈጽምልሽ ዘንድ ጸሎቴ አይለይሽም፡፡ የጀመርሽው መንፈሳዊ ጉዞ በእግዚአብሔር የተፈቀደ በመሆኑ ያለጥርጥር ይሳካል›› ሲሉ አባ ለወይዘሮ ድንቃየሁ ቡራኬ ሰጥተው አሰናበቷቸው፡፡ በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻል የለ፡፡

 ወይዘሮ ድንቃየሁ ሕልም ማየታቸውን አላቋረጡም፡፡ አንድ ቀን አባ ይትባረክ የተባሉ መነኩሴ ከሩቅ ቦታ መጥተው በወላጆቻቸው ቤት የእግዚአብሔር እንግዳ ብለው ይገባሉ፡፡ እማሆይም እራታቸውን አብልተው እግራቸውን አጥበውና ምኞታቸውን አዘጋጅተው እንዲያድሩ ያደርጋሉ፡፡
 የአባ ይትባረክ ወደዚያ አካባቢ መምጣት የተለመደ ነበር፡፡ ከስምንት ዓመት በፊት በወይዘሮ ድንቃየሁ አባት የተጀመረውን የቅዱስ ቂርቆስ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለማሠራትና ሕዝቡን ለማስተማር ብዙ ጊዜ ተመላልሰዋል፡፡

 ይሁን እንጂ የቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ሳይጀመር ይቀራል፡፡ የወይዘሮ ድንቃየሁ ወላጅ አባትና አባ ይትባረክ የተነሱለት ዓላማ ባለመሳካቱ ተስፋ ቆርጠው ጊዜ ይጠብቃሉ፡፡ አባ ይትባረክ በእንግዳነት ባደሩበት ሌሊት ወይዘሮ ድንቃየሁ ሕልም ያያሉ፡፡ ሕልሙ ወይዘሮ ድንቃየሁ ወደ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን እየሔዱ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ አዘውትረው የሚሔዱቡት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ መግቢያ በር ላይ እንደደረሱ ሦስት ሰዎች ቀድመዋቸው በቀጥታ ወደ መቅደስ ይገባሉ፡፡ ከዚያም ወይዘሮ ድንቃየሁ ተከትለው ለመግባት ሲሞክሩ በሩ ላይ ሁለት እርጉዝ ሴቶች ለመውለድ ምጥ ተይዘው ያገኛሉ፡፡

 ሁለቱን ሴቶች ምጥ ተይዛችሁ ለምን እዚህ መጣችሁ? እያሉ በመጠየቅ ላይ እንዳሉ ሴቶቹ ይገላገላሉ፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁ አሁን ተገላግላችኋል፡፡ ምስጋና ለአምላክ ይሁን፡፡ ተነሱና የማርያም መሸኛ እናዘጋጅ ይሏቸዋል፡፡ ሁለቱ አራስ ሴቶች እኛ ማተብ ሳናስር ከዚህ አንወጣም በማለት ለመውጣት ፈቃደኛ አልሆኑም፡:

ወይዘሮ ድንቃየሁ እምቢ ሲሏቸው ከቤተ ክርስቲያኑ ወጥተው ወደ ቤታቸው ለመሔድ ጉዞ ሲጀመሩ አንድ ወጣት ቀይ ግምጃ የለበሰ ወጣት ጠርቶ ያስቆማቸዋል፡፡ ከዚያም ሰውየው ወደ አጠገባቸው ይቀርብናእንኪ ይህን መስቀል ለአባ ይትባረክ ስጫቸው፡፡ይላቸዋል፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁእኔ ቄስ ወይም ዲያቆን አይደለሁም፡፡  

መስቀል እንዴት እይዛለሁ?” በማለት እምቢታቸውን ይገልጻሉ፡፡ ሰውየው አሁንም ጥያቄውን እየደጋገመ ያስቸግራቸዋል፡፡ ወዲያውአባ ይትባረክን መስቀሉን ይዘህ ቤተ ክርስቲያን ሦስት ጊዜ እየዞርህ ባርከው የታሰበው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ይሠራል፡፡ የተቀበረውም ይመክናል ብለሽ ንገሪው፡፡ብሎ መልእክቱን እንደነገራቸው ከእንቅልፋቸው ይነቃሉ፡፡

ጥዋት ቀደም ብለው አባ ይትባረክና ወይዘሮ ድንቃየሁ ወደ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን ለኪዳን ሲሄዱ ሌሊት ያዩትን ሕልም ለአባ ይትባረክ ይነግሯቸዋል፡፡ አባ ይትባረክ በጥሞና ካዳመጡ በኋላ ትርጉሙን ለወይዘሮ ድንቃየሁ ይነግራሉ፡፡ትርጉሙም የተገላገሉት እኛ የደከምንበት፣ ብዙ ያሰብንበት የዚህ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ሥራ ከዳር መድረሱን እኛም ከሀሳብ መገላገላችንን የሚያመለክት ነው፡፡ የታሰበው በሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ መጀመርና መጠናቀቅም አንቺን አምላክ ምክንያት ያደርጋል፡፡ በአንቺ ቅስቀሳና ማስተባበር የሕዝቡ ልቡና ቀንቶ አሳባችን ይሳካል፡፡በማለት ተረጎሙላቸው፡፡

 በሚቀጥለው የሰንበት ቀን ሕዝቡ በተሰበሰበበት አባ ይትባረክና ወይዘሮ ድንቃየሁ የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ የሚጀመርበትን ሀሳብ ለቀበሌው ሕዝብ ያቀርባሉ፡፡ ሕዝቡም በአንድ ልብ አስቦ በአንድ መንፈስ ተመካክሮ ለስምንት ዓመት ሲጓተት የቆየው ሥራ እንዲጀመር አስተባባሪ ሽማግሌዎችን ሰይሞ ይለያያል፡፡

 የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ ሥራ ተጀመረ፡፡ ወይዘሮ ድንቃየሁ የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ሥራ አደራ ከአምላክና ከቀበሌው ሰበካ ጉባኤ ሕዝብ ከተቀበሉ በኋላ እርዳታ ለማሰባሰብ በተለያዩ ከተሞች ጥረታቸውን ቀጠሉ፡፡

የአካባቢው አርሶ አደሮችም በገንዘባቸው፣በጉልበታቸው ሙሉ ትብብር በማድረግ የቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ሥራ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ተመረቀ፡፡

 የቅዱስ ቂርቆስ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በአጭር ጊዜ መጠናቀቁን የተመለከተው የጎረቤት ቀበሌ ማለትም የግራራም ማርያም ሕዝብም ለእማሆይ ወለተ ማርያም ጥያቄ አቀረበ፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በዕድሜ ብዛት ማርጀቱንና በአዲስ መልክ መሥራት አስፈላጊ በመሆኑ፤ ለዚህም ሥራ ወይዘሮ ድንቃየሁ እርዳታ እንዲያስተባብሩላቸው ይጠይቃሉ፡፡  

እሳቸውም ሕዝብ በተሰበሰበበት የሕንፃ ቤተ ክርቲያኑን ሥራ ለማስተባበር እርዳታም የሚቻላቸውን ሁሉ ለማፈላለግ ቃል ይገባሉ፡ የአምላክ ፈቃድ ታክሎበት የግራራማ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ይመረቃል፡፡

 ወይዘሮ ድንቃየሁ በሕልማቸው ሁልጊዜ የሚያዩት ተራራ፣ደን፣ዋሻ ነበር፡፡ ዋሻው በደን (የወደፊቱ እየታያቸው) የተከበበና አራዊት የሚኖሩበት፣ የተለያዩ ጅረቶች የሚፈሱበት፣ በተራሮች አካባቢ እንደሚገኝም ይታያቸዋል፡፡የት ይሆን?” እያሉ ያስቡ ነበር፡፡ 

 ያዩትን ሕልም መሠረት አድርገው የአካባቢውን ነዋሪዎችንእንዲህ ዓይነት ቦታ አለን? በግራራም ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ክልል ውስጥ ይገኝ ይሆንን?” ብለው ጠየቁ፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎችምአዎንብለው ቦታውን ሊያሳይዋቸው ይዘዋቸው ሄዱ፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞም ያዘጋጀው ቦታ ስለሆነ ገና ሲያዩት የቦታውን ክብር ተረዱ ሕልማቸውም እውነተኛ ሆነ፡፡

 እማሆይ ወደ ገዳሙ ሲደርሱ የአካባቢው ሰዎችም ወደ ቤታቸው ሄዱ፡፡ ጅብና የነብር መንጋዎች ግን እማሆይን ሳያተናኮሉ ያላምዷቸው ነበር፡፡እማሆይ የአራዊቱ በቦታው መኖር አላስፈራቸውም፡፡ በእምነታቸው ጸንተው በጻድቃን ሰማዕታትና በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ጥበቃ በጫካ ውስጥ ያሉ አራዊቶች በሙሉ ተገዙላቸው፡፡ የእግዚአብሔር ክብር የሚገለጽበት ቦታ በመሆኑ እግዚአብሔር እማሆይን መንገድ ጠራጊ አደረገ፡፡

 ዋሻዎቹ በጥንት ዘመን ሰዎች ከጦርነት ወረራና ጥቃት ለማምለጥ ይጠለሉበት የነበረ መሆኑን አንዳንድ ካህናት ይጠቁማሉ፡፡ ዋሻው ውስጥ የእህል ማከማቻ ጎተራ የምግብ ማብሰያ ሸክላና ማገዶ እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁስ ተገኝተዋል፡፡

 ከዋሻው አናት በላይ ከረጅም ርቀት እየተወረወሩ ቁልቁል የሚፈሱት ጅረቶች መውረጃ መንገዳቸውን ስተው ወደ ዋሻው ውስጥ በመፍሰሳቸው ዋሻው በደለል ተሞልቷል፡፡ ዋሻውን ከደለል አጽድቶ ቅርጽ እንዲይዝ የእማሆይ ቀጣዩ ተግባር ነበር፡፡ ለዚህ ሥራ የአካባቢውን ሕዝብ በማስተባበር ደለሉ ተጠረገ፡፡ እማሆይም መኖሪያቸውን ከአራዊት ጋር አደረጉ፡፡

 እማሆይ ወለተ ማርያም ደለል ጠርገው መኖሪያ ባደረጉት ዋሻ ውስጥ ቀድመው ይኖሩ የነበሩ የተለያዩ የዱር አራዊት ማታ ከጫካ ሲመለሱ፣ ጥዋት ወደ መዋያቸው ሲሰማሩ በእማሆይ ላይ ምንም ጥቃት አላደረሱም፡፡ በድምፁ የረበሸ፣ ፀጥታ የነፈገ አውሬ ሳይኖር እማሆይና አራዊቱ ዓይን ለዓይን እየተያዩ ለሁለት ዓመታት በሠላም አብረው ቆዩ፡፡

 ከሁለት ዓመታት የጋራ ኑሮ በኋላ አራዊቱ ዋሻውን ለእማሆይ የብቸኝነት መኖሪያ ለቅቀውላቸው ወደ ሌላ አካባቢ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተሰደዱ፡፡እንዲህ አሉ እማሆይአንድ ቀን ጅቦቹና ነብሮቹ ተሰበሰቡ የዛን ቀን ልዩ ነገር አየሁ፤ መሬቱን ጫሩ፣ጮኹ፣አለቀሱ፡፡ ጩኸታቸው እንደዛ ቀን አስፈርቶኝ አያውቅም፡፡ ወዲያው ገዳሙን ለቀው ሄዱ፡፡ ያኔ ፈራሁ አለቀስኩ፡፡ 

 ጓደኞቼ ነበሩና ሲለዩኝ አዘንኩ፡፡እማሆይ በዚህን ጊዜ ነው የበለጠ የተጨነቁት፡፡ የአራዊቱ መውጣትና መግባት መቆም ለእማሆይ አሳሳቢ ፈተና ነበር፡፡ አራዊቱ ጥዋትና ማታ ሲወጡና ሲገቡ ለእማሆይ እንደ ቅርብ ዘመዶቻቸው ፍቅር አሳድረዋል፡፡ በዓይን በመተያየት ተላምደዋል፡፡ ባለመጣላታቸውና ጉዳት ለማድረስ ባለመሞከራቸው አራዊቱ ለእማሆይ ታላቅ ባለውለታዎች ሆነዋል፡፡ ኀጥዕ ማንም ሳያሳድደው ይሸሻል፡፡ ጻድቅ ግን እንደ አንበሳ ያለፍርሃት ይኖራል፡፡ እንዳለ መጽሐፈ ምሳሌ፡፡

 እማሆይ ወለተ ማርያም ለሁለት ዓመታት በዋሻው ውስጥ ከቆዩ በኋላ በወቅቱ ወደ ነበሩት ወደ ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዘካርያስ እርዳታ ጠየቁ፡፡ ለሊቀ ጳጳሱ ስለ ዋሻው ምንነትና የወደፊት መንፈሳዊ ፀጋ አስረዱ፡፡ በመጨረሻም ሊቀ ጳጳሱ ዋሻውን እንደሚያዩላቸው ቃል ገቡላቸው፡፡ በቃላቸው መሠረትም ወደ አካባቢው ተጉዘው ዋሻውንና አካባቢውን ከተመለከቱ በኋላይህማ ገዳመ ቆሮንቶስ ነው፡፡ብለው እማሆይ ምን እንደሚፈልጉ ጠየቁ፡፡ እማሆይ ወለተ ማርያምምየእግዚአብሔር መልካም ፈቃዱ ቢሆን እኔ የምመኘው የአባታችንን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትንና የቅዱስ ዑራኤልን ጽላት ቢገባልንና ቢገደምአሉ፡፡

 የምሥራቅ ጎጃም ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዘካርያስ መልካም ፈቃዳቸው ሆኖ ግንቦት 22 ቀን 1987 . የተጠየቁትን ጽላቶች ይዘው ወደስፍራ በመሄድ ጽላቶቹን አስገብተው ገዳም መሆኑን አበሠሩ፡፡ በአካባቢው ሕዝብ ዘንድ ታላቅ በዓል ተደረገ፡፡ በዕለቱ የቅዱስ ዑራኤልና የአባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፀበሎች ተባርከው ለሕዝቡ አገልግሎት መስጠት ጀመሩ ፡፡ 

 እማሆይ ገዳሙን አስፍተው፤ሥርዐተ ገዳሙን አጠናክረው በልማት መስክ ተሰማርተው ሳለየቅዱስ ዑራኤልን ቤተክርስቲያን ብንሠራብለው አሰቡ፡፡ የመንፈስ ልጆቻቸውን አማከሩ፡፡ በገዳሙ የተፈወሱ ወንድሞች ዲዛይኑን ሠርተው በማስረከባቸውና ገንዘብ በማሰባሰባቸው እማሆይም አዲስ አበባ ድረስ በመሄድ ለህንጻው የሚሆን የግንባታ ዕቃ በማሰባሰብ በአጭር ጊዜ ቤተክርስቲያኑ ተሠርቶ አለቀ፡፡

 ቤተክርስቲያኑን ድንገት ለሚያየው እጅግ ያማረ ሆኖ ደኑን ከጀርባው አድርጎ የበቀለ የሚመስል እጅግ የሚማርክና መንፈስን የሚያድስ ነው ፡፡ በዚያ ቦታ ያንን የመሰለ ቤተክርስቲያን መሠራቱ በእናቶቸ አስተባባሪነት፡፡ ያውም ፊደል ባልቆጠረ፡፡ እኔ ባየሁት ሁሉ ነፍሴ ረክታለች፡፡ ተስፋዬም ለምልሟል፡፡ደግ ሰው! የሃይማኖት ሰው! ታታሪ ሰው! እግዚአብሔር አላሳጣንምና፡፡ ገዳሙን ያስፋልን ሺህ እልፍ ያድርግልን፡፡

 እማሆይ የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበራት ቅንጅት ድርጅት ተምሳሌት ዕጹብ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ሴቶች በሚለው መጽሐፍ ላይ በደን ልማት፣ በባዮ ጋዝና በትጋታቸው ከታዋቂ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ጋራ ሥራቸውን አቀርቧል፡፡

ተጻፈ ታኅሣሥ 8 ቀን 2007 ዓ.ም.
በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ



Featured post

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

                    የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደር...