![]() |
| Two koreans |
ሰሜን
ኮርያ ሰሞኑን ያልተለመደ አዲስ መልዕክት
በብሔራዊ የቴሌቪዥ ጣቢያዋ አማካኝነት
አስተላልፋለች። ቀድሞም አንደ አንድ አገር
ከነበሩት ደቡብ ኮሪያ ጋር የእንቀላቀል ፍላጎት
ጥያቄ ማቅረቧ ግን በርካቶችን ያስገረመ ነበር።
ከጣቢያው በወጣው መረጃ መሰረት በአገራቸው
እና ከአገራቸው ውጪ የሚገኙ ሁሉም ኮሪያውያን
ከሌላ አገራት ድጋፍ ውጩ በሆነ መንገድ
አንድነታቸውን ማረጋገጥ እነደሚገባቸው
የሚያሳስብ መዕክልት ተላልፏል።
እንደ
መረጃው ከሆነ፤ በሁለቱ ኮርያውያን መካከል
ነጻ የሆነ በአንድነት ለመመስረት መነሳሳት
ያስፈልጋል የሚል ያልተጠበቀ መልዕክት በብሔራዊ
ጣቢያው አማካኝነት ተላልፏል። ኮሪያውያን
የጦርነት ስጋቶችን ወደ ጎን በመተው ኮሪያ
ሰርጥን ሰላማዊ ቀጣና ለማድረግ መነሳሳት
እንዳለባቸው አሳስቧል።
የጣቢያው
መረጃ የተለቀቀው በአገሪቷ መንግስት እና
ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ካካሄዱት ውይይት
በኋላ እነደነበር እማኞች ይገልጻሉ። ብሔራዊ
ጣቢያው የአገራቱ ዜጎችም ገንኙነታቸውን
በማጠናከር ከሰሜን ወደ ደቡብ እነዲሁም ከደቡብ
ወደ ሰሜን ኮሪያ አገራት ጎዞ ማካሄድን መልመድ
እንደሚገባቸው ምክር አዘል መልዕክቱዝን
አሰራጭቷል።
በመጨረሻም
ያስተላለፈው መረጃ ግን ማስጠንቀቂያ አዘል
ቃላትን የያዘ ነበር። በመጨረሻዎቹ አረፍተ
ነገሮች ላይ የሁለቱን አገራት ውህደት ሊያደናቅፍ
የሚችል ማንኛውንም አይነት ችግር በማጥፋት
ፒዮንጊያንግ ቁርጠኛ ስለመሆኗን ነበር
ማስጠነቀቂያው የተላለፈው። ይህ የማገባደጃ
መልዕክት ግን በብዙዎች ዘንድ በቸልታ አልታለፈም።
የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ፤
የማሳረጊያው መልዕክት የሰሜን ኮርያ መንግስትን
እብሪተኝነት መቼም የሚያባራ አለመሆኑን
ያሳያል። ምክንያቱም በሁለቱ ኮሪያዎች መካከል
ከፍተኛ የፖለቲካ ውጥረት እንዲከሰት ያደረገው
የሰሜን ኮሪያ በአካባቢው የምታደርገው ወታደራዊ
እንቅስቃሴ መሆኑ ተዘንግቷል። በቃጣናው ላይ
የሚደረጉ የኒኩሌር እና የሚሳኤል ሙከራዎች
የአካባቢውን ውጥረት አባብሰው አገራቱ መልካም
ግንኙነት እንዳያደርጉ እክል መፍጠሩንም
በርካቶች ይስማሙበታል።
እ.አ.አ.
በ1948
ሰሜንና
ደቡብ ኮሪያ በሚል ሁለት አገሮች ከተፈጠሩ
በኋላ ደም አፋሳሽ ጦርነት
መካሄዱን ታሪክ ያስረዳናል። ከ1950
እስከ
1953
የተካሄደው
የኮሪያ ጦርነትን
የሁለቱን መለያየት ይበልጥ እንዲሰፋ ያደረገ
ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡
በጦርነቱ ላይ ሰሜን ኮሪያ
ወረራ ማካሄዷን በመቃወም ኢትዮጵያን ጨምሮ
በርካታ አገራት ከደቡብ ኮሪያ ጎን ተሰልፈው
ውጊያ ማካሄዳቸውም ይታወቃል። በተለይም
በጦርነቱ ላይ አሜሪካ እና
የቀድሞዋ ሶቪዬት
ህብረት ከፍተኛ
ፖለቲካዊ ሚና እንደተጫወቱ
የአካባቢው ፖለቲካ ምሁራን ይገልጻሉ።
ሰሜንና
ደቡብ ኮርያ ለሶስት ዓመታት ባደረጉት
ጦርነት ኢኮኖሚያቸው ከፉኛ የተጎዳ ሲሆን፤
አገራቱን ወንድማማች ህዝቦች ያቀያየመ ነበር።
ጦርነቱ ከሶስት ሚሊየን በላይ የሰው ህይወት
መጥፋቱ፣ በሚሊዮኖች የሚጠጉትን ደግሞ ለአካል
ጉዳት እንዲሁም አስር ሚሊኖች ዜጎች ከቤተሰቦቻቸው
ጋር እንዲለያዩ ምክንያት ሆኗል። በዚህም
ምክንያት በአስከፊነቱ በአለም
ላይ ከሚጠቀሱ ጦርነቶች መካከል የሚመደብ
ነው። በርካቶችን
ለሞት እና ለመፈናቀል የዳረገው የኮሪያ ልሳነ
ምድር ጦርነት
ከተገባደደ በኋም አገራቱን መልሶ ወደ አንድነት
ሊያመጡ የሚችሉ በርካታ ውይይቶች በተለያዩ
ጊዜያት ተካሂደዋል። አለም አቀፍ አደራዳሪዎች
ጭምር የተካፈሉባቸው የእርስ በእርስ ውይይቶች
ተደርገዋል። ነገር ግን ውይይቶቹ
መጨረሻቸው ውጤት
አልባ በመሆኑ ምክንያት አገራቱን ለማዋሃድ
የተደረጉ ሙከራዎች በሙሉ ሊሳኩ አልቻሉም።
ከቅርብ
አመታት ወዲህ ደግሞ የሰሜን ኮሪያ የኒኩሌር
እና ሚሳኤል መሳሪያዎች ሙከራ አገራቱን ዳግም
ወደ ጦርነተ እንዳያመሩ ስጋት የጫረ ጉዳይ
ነበር። ሰሜን ኮሪያ ከዚህ ቀደምም በተለያዩ
ጊዜያቶች ጎረቤቷን ደቡብ ኮሪያን፣ አሜሪካንን
እና የተለያዩ የእስያ አገራትን በፕሬዝዳንቷ
ኪም ጁንግ ኡን አማካኝነት ስታስፈራራ አልፎ
ተርፎም የኒኩሌር ማብላዋ ውስጥ ያበለጸገችውን
መሳሪያ እየሞከረች እራሷን ለጦርነት ስታዘጋጅ
መቆየቷ የሚታወስ ነው። የኮሪያውያኑ ልሳነ
ምድርም በአለም ሃያላኑ አገራት አሜሪካ፣
ሩሲያ፣ ቻይና እና የተለያዩ የእስያ አገራት
የፖለቲካ የበላይነት ለማስጠበቅ በሚደረግ
ፉክክር መሃል ገብቶ ቆይቷል። በተለይ በዶናልድ
ትራምፕ ፕሬዝዳንትነት የምትመራው አሜሪካ
በተለያዩ ጊዜያት የሰሜን ኮሪያን እብሪተኛ
መንግስት ለመቅጣት እና እራሷን ከማንኛውም
ጥቃት ለመከላከል አስፈላጊውን መታደራዊ
ልምምድ እያደረገች መሆኑን ትገልጻለች።
በኮሪያውያኑ
ልሣነ ምድር የተደራጀ ወታደራዊ የጦር ሠፈር
ያላት አሜሪካ ከወዳጆቿ ከጃፓን እና ደቡብ
ኮሪያ ጋር የተቀናጀ የባህር እና የየብስ
ወታደራዊ ልምምዶችን ማካሄዷነ ቀጥላለች።
በየአመቱም በቀጣናው ከሚገኙ አጋሮቿ ጋር
የሁለት ሳምንታት ግፋ ሲልም ለወራት የዘለቀ
ወታደራዊ ልምምድ የምታደርገው አሜሪካ ልምምዱ
በማንኛውም ጊዜ ሊሰነዘር የሚችል የሰሜን
ኮሪያን ጥቃት ለመከላከል እና የአገሯን
እንዲሁን የአካባቢውን ደህንነት ለማስጠበቅ
አላማ ያደረገ መሆኑንም ትገልጻለች።
አልፎ
አልፎ ግን ከደቡብ ኮሪያ እና ሰሜን ኮሪያ
ድንበሮች ላይ ለቅኝት በሚል ሰበብ የሚያንዣብቡ
የአሜሪካን የጦር ተዋጊ ጄቶች ሰሜን ኮሪያን
ከማስቆጣቱም አልፉ የሁለቱ ኮሪያውያኖችን
የሻከረ ግንኙነታቸውን ዳግም እንዳያንሰራራ
ሲያደርግ የቆየ እንቅስቃሴ ነው። ሰሜን ኮሪያ
የአሜሪካ ከደቡብ ኮሪያ ጋር የተያያዘ ወታደራዊ
ልምምድ ማከናወኗ ወደለየለት ግጭት ሊያመራ
የሚችል በር ከፋች ነው በማለት ማስጠነቀቂያዋን
ስትሰጥ ሰንብታለች።
በዚህም
ተባለ በዚያ ግን የሁለቱ ኮሪያውያን ወዳጅነት
በእራሳቸው መካከል ከተደረገ ጦርነት በተጨማሪ
የአለም ኃያላን አገራት በሚያደርጉት ፖለቲካዊ
ጨዋታ ምክንያት እየተቀዛቀዘ መሄዱ ገሃድ
የወጣ እውነታ ነበር። ከዚህ ሁሉ እሰጥ አገባ
በኋላ ሰሜን ኮሪያ የእንዋሃድ መልዕክት
ማስተላለፏ ብዙዎችን ያስገረመ ሆኗል። ይህ
የእንዋሃድ መዕክት ግን በአጋጣሚ የመጣ
እንዳልሆነ የሚከራከሩም አልጠፉም። ከቅርብ
ወራት ወዲህ ሰሜን እና ደቡበ ኮሪያ በስፖርቱና
በኪነጥበበ መስኮች በጋራ ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን
ስምምነቶች ሲያደርጉ መቆየታቸውንም የውህደት
ጥያቄው ከመሬት የተነሳ ድንገተኛ ጉዳይ
አለመሆኑን እንደ ምክንያትነት ይቀርባል።
የተለያዩ
የመገናኛ ብዙሃን ሲዘግቡ እንደቆዩትም ሰሜንና
ደቡብ ኮርያ ከበርካታ ዓመታት የተዘጋ ግንኙነታቸው
በኋላ በኪነጥበቡ መድረክ ላይ ዳግም ለመገናኘት
ፍላጎት እንዳላቸው ይፋ አድርገዋል። በቀጣይ
ጊዜያት በደቡብ
ኮርያዋ ርዕሰ መዲና ሴኡል በሚዘጋጀው የባህል
እና የኪነጥበብ ልምድ ልውውጥ የጋራ መድረክም
ላይ የሁለቱም አገራት ህዝቦች እንደሚካፈሉም
ይጠበቃል። ዝግጅቱም በአገራቱ መካከል መልካም
ግንኙነት ለመጀመር በር የሚከፍት ሂደት መሆኑን
እየተገለጸ ይገኛል።
በሌላ
በኩል የሁለቱ አገራት የስፖርት ውህደት ከወዲሁ
አድናቆት እየተቸረው መጥቷል። ሰሜን
ኮርያ ቀጣዩ ወር በደቡብ ኮርያዋ ፒዮንግያንግ
ለሚካሄደው የክረምት ኦሎምፒክ ውድድር የከፍተኛ
ደረጃ ልዑካን ቡድኗን ለመላክ ስምንነት
አድርጋለች። የሰሜን እና ደቡብ ኮርያ ኃላፊዎች
እና የስፖርት ሰዎች ተገናኝተው ከተነጋገሩ
በኋላ ሰሜን ኮርያ የከፍተኛ ልዑካንን ቡድኗን
ወደስፍራው ፣ እንደምትልክ በኃላፊዎች በኩል
መግለጫ ሰጥታለች። ከዚህ በኋላ በተደረጉ
ስምምነቶች ደግሞ በክረምቱ ኦሎምፒክ ከሚላኩ
ስፖርተኞች መካከል በጤቶቹ የበረዶ ላይ ገና
ጨዋታ ከአገራቱ የተውጣጡ ተጫዋቾች በአንድ
ቡድን በጋራ ተወክለው እንደሚጫወቱ ይፋ ሆኗል።
ከዚህ
በተጨማሪም በኦሎምፒኩ የመክፈቻ ስነስርዓት
ወቅት አገራቱ በአንድ ሰንደቅ አላማ ስር
እራሳቸውን በማስተዋወቅ በህዝብ ፊት እንደሚተዋወቁ
ቃል ተገብቷል። ውድድሩም ከሁለት ሳምንታት
በኃላ እ.አ.አ.
የካቲት
ዘጠኝ ቀን 2018
የሚጀመር
በመሆኑ በርካቶች የአገራቱን የአንድነት
ትዕይንት ለመመልከት ጓጉተዋል። ከስፖርትና
ከኪነጥበድ ውህደቶቹ በተጨማሪ የሰሜን ኮሪያ
የአንድነት ጥያቄ መቅረቡ አገራቱ በጋራ
ለመንቀሳቀስ እድል እንዳላቸው አመላካች ነው
የሚል ተስፋን ኮሪያዎች እንዲሰንኩ ምክንያት
ሆኗል።
ጥቂት
የማይባሉ የደቡብ ኮሪያ ዜጎች ግን የሰሜን
ኮርያው ፕሬዝዳንት እብሪተኛነት እና በየጊዜው
የሚወረወሩ የጦርነት ቃላት ግንኙነቱ ወደ
ውህደት እንዳያመራ እክል የሚፈጥር ነው የሚል
ፈጥሮባቸዋል። የዘርፉ ፖለቲካ ተንታኞች
እንደሚሉት ደግሞ ከበርካታ አመታት ጦርነት
እና የፖለቲካ ፍጥጫ በኋላ ለውህደት ጅማሮ
የሚፈጥሩ ጉዳዮች መከሰታቸው አገራቱን ወደ
አንድነት የማያመራ ቢሆን እንኳን በመካከላቸው
መልካም ግንኙነት እንዲኖር እድል የሚፈጥር
አጋጣሚ ይፈጥራል።

