Thursday, May 19, 2022

በኦሮሚያ ከሕግ ውጪ የታሰሩ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባላት በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ ጠየቀ

 የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ በኦሮሚያ፡ ከሕግ አግባብ ውጪ በእስር ላይ የሚገኙ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባላት በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቁ ይገባል፤ ሌሎች የቅድመ-ክስ ታሳሪዎችም ተዓማኒ ክስ ካልቀረበባቸው በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቁ ይገባል ብሏል

የተራዘመ ቅድመ-ክስ እስር (prolonged pre-trial detention) ሰዎች በፍትሕ አስተዳደር ላይ ያላቸውን እምነት ያጠፋል ሲል አሳስቧል።

 

ኢሰመኮ በተለያዩ ፖሊስ መምሪያዎች በእስር ላይ ያሉ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባሎች የእስር ሁኔታን በተመለከተ ለረጅም ጊዜ ሲያደርገው ከነበረው ክትትል በተጨማሪ ከፓርቲው እና ከእስረኞች ቤተሰቦች ቀረቡ አቤቱታዎች መነሻነት ከመጋቢት 1 እስከ 10 ቀን 2014 ዓ.ም. በቡራዩ ከተማበገላን ከተማ እና በሰበታ ፖሊስ መምሪያዎች በአካል በመገኘት ክትትል ማድረጉን ገልጿል።

በዚህም እስረኞችን፣ የፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎችን፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንእና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ግ ተወካዮችን በማነጋገር ምርመራ ማድረጉን አስታውቋል።

 

በተጨማሪም በተለያዩ ጊዜያት እስረኞቹን በሚመለከት በፍርድ ቤት እና በዐቃቤ ግ የተሰጡ ውሳኔዎችእና ትዕዛዞችን እንዲሁም የክምና ሰነዶችን መመልከቱን አሳውቋል።

በቡራዩ ፖሊስ መምሪያ በእስር ላይ የነበሩ አቶ ሚካኤል ጎበና፣ አቶ ኬኔሳ አያና፣ ዶ/ር ገዳ ወልጅራ፣ አቶ ዳዊት አብደታ፣ አቶ ለሚ ቤኛ፣ አቶ ገዳ ገቢሳ የተባሉ የፓርቲው አመራር መሆናቸውን የገለጹ ስድስት እስረኞችን ኮሚሽኑ አነጋግሯል። በተጨማሪም ኮኔል ገመቹ አያና በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ማዕከል፣ እንዲሁም አቶ አብዲ ረጋሳ ገላን ከተማ በሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ልዩ ፖሊስ ካምፕ ውስጥ በእስር ላይ የሚገኙ መሆኑን ከቤተሰብ እና ከጠበቆቻቸው መረዳት መቻሉን ጠቁሟል።

በተመሳሳይ አቶ በቴ ኡርጌሳ በእስር ላይ እያሉ ባጋጠማቸው ሕመም ምክንያት በፖሊስ ዋስትና ፈቅዶላቸው በአንድ የሕክምና ተቋም ሕክምና ላይ የነበሩ መሆኑን ኮሚሽኑ መመልከቱን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህ ምርመራ መሰረት፣ ፍርድ ቤት በዋስትና እንዲለቀቁ የፈቀደላቸው፣ የክስ መዝገቦቻቸው ተዘግተው በፍርድ ቤት ውሳኔ በነ የተሰናበቱ ምንም አይነት ክስ ያልተመሰረተባቸው እና ዐቃቤ ግ ክስ የማይመሰርትባቸው መሆኑን በማረጋገጥ የምርመራ መዝገባቸው የተዘጋ፤ ሆኖም ከወራት እስከ 2 መት ለሚሆን ጊዜ በተለያዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ ከሕግ አግባብ ውጪ በእስር ላይ የሚገኙና የተወሰኑትም በእስሩ ሂደት በተፈጸመ ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እና ድብደባ ለተለያዩ የአካል ጉዳቶችና የጤና እክል የተጋለጡ እስረኞች መሆናቸውን ኢሰመኮ መረዳቱን ገልጿል።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “የኦነግ ፓርቲ አመራሮች ለተራዘመ ጊዜ ከሕግ አግባብ ውጭ ታስረው የሚገኙ በመሆኑ በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቁ እና ለደረሰባችው ጉዳት ሊካሱ የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም “የፍርድ ቤትና የዐቃቤ ሕግ ውሳኔዎች በተደጋጋሚ እየተጣሰ እስረኞቹ ከሕግ ውጪ ለተራዘመ እስር መዳረጋቸው ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም ስለሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አፋጣኝ ማጣራት አካሂዶ ተገቢውን እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል” ብለዋል፡፡

የኢሰመኮ የሲቪል፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጂብሪል በበኩላቸው “በተለይም ታሳሪዎቹ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በመሆናቸው በሕዝባዊ አገልግሎት ስራቸው ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት እንዳይጋለጡ ጥበቃ ሊደረግ ሲገባ፤ በተግባር የተገላቢጦሽ መሆኑ አሳዛኝ መሆኑን አስታውሰው ጉዳዩ አፋጣኝ እልባት ያስፈልገዋል” ሲሉ አሳስበዋል።

 

Monday, May 16, 2022

MOFA Ethiopia congratulates President H.E. Hassan Sheikh Mohamud

 

The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia warmly congratulates former President H.E. Hassan Sheikh Mohamud on his reelection as President of the Federal Republic of Somalia.

 

                                                                                Logo of the Ethiopian Foreign minister

As announced on the official page of the Ministry, Ethiopia believes that the election demonstrates the confidence of the people of Somalia in you and is a leap forward to building a democratic process in the country. 


 

 

         Hassan Sheikh Mohamud,  President of the Federal Republic of Somalia.

 

The Ministry said, on behalf of the Government and people of Ethiopia looks forward to working with President Hassan Sheikh Mohamud and his administration in the spirit of the longstanding and friendly relationship between Ethiopia and Somalia.

The Ministry extends best wishes for your Excellency's well-being and the peace and prosperity of the people of Somalia.

PM Abiy Ahmed Ali on Twitter says "I would like to congratulate former President Hassan Sheikh Mohamud on being re-elected as the President of the Federal Republic of Somalia. I look forward to working closely with you on common bilateral and regional interests".

Featured post

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

                    የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደር...