Saturday, December 9, 2017

Traditional Medicine In Ethiopia

Plants have been used as a source of medicine in Ethiopia from time immemorial to treat different ailments. This is often linked to ethnic and cultural diversity coupled with an array of unique flora and fauna that are employed as the prime-tools in the fight against numerous health problems. Even with the advent of modern medicine, this indigenous health care delivery system is the major source of care for an estimated 80% of the population. More than 95% of traditional medical preparations are of plant origin The Ethiopian flora is estimated to contain between 6500 and 7000 species of higher plants of which about 12% are endemic. The Directorate of Traditional and Modern Medicine (TMMRD) within EPHI conducting operational and basic research on the quality, efficacy and safety of traditional and modern medicine including the factors affecting the rational utilization and factors determine drug resist stance for the major health problems of the country.

Friday, December 8, 2017

የኤሌክትሪክ ፍጆታ ስሌት ልዩነት አለውን?

አቶ መንግስቱ አለሙ በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ናቸው። በመኖሪያ ግቢያቸው ውስጥ አንድ አነስተኛ የፍራፍሬ መሸጫ ሱቅ እና አምስት መኖሪያ ቤቶች ይገኛሉ። የፍራፍሬ መሸጫ ሱቋን ገንብተው ካከራዩ አስር ወራት የተቆጠረ ቢሆንም ከሶስት ወራት ወዲህ ግን የኤሌክትሪክ ወጪያቸው እያየለ መምጣቱን ይናገራሉ። በተለይም ከአራት እና አምስት ወራት በፊት ይከፍሉ የነበረው 500 ብር ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ በተከታታይ ለሶስት ወራት ከእጥፍ ላይ 1500 ብር የሚጠጋ ገንዘብ አስወጥቷቸዋል። ለንግድ ቤቱ እና ለመኖሪያ ቤቶቹ የሚጠቀሙበት አንድ ቆጣሪ ቢሆንም የክፍያ ጭማሪውን ምክንያቱን ለማወቅ ይጥራሉ። በተከራዮች ከፍተኛ ፍጆታ የተከሰተ መሆኑን ለማጣራትም ሌት ተከን ቢታትሩም ምንም አይነት የአጠቃቀም ለውጥ በተከራዮቻቸው ላይ ሊያገኙ አልቻሉም።
ጉዳዩን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ሲዘዋወሩ ግን በግቢያቸው ውስጥ አንድ የንግድ ሱቅ በመኖሩ ምክንያት የኤሌክትሪክ ፍጆታ አቆጣጠሩ ከመደበኛ መኖሪያ ቤት ወደ ንግድ ቤት ታሪፍ መቀየሩ ይነገራቸዋል። ከሶስት ወራት በፊት ጀምሮ በቆጣሪ አነባበብ ላይ የተደረገው የአሰራር ለውጥ በእያንዳዱ የንግድ ቤት ያለው ግለሰብ ላይ የሚደረግ አሰራር መሆኑም ይነገራቸዋል። አቆጣጠሩ የተቀየረውም ቆጣሪ አንባቢዎች ባደረሱት መረጃ መሰረት መሆኑን እና ቀደም ብሎ ንግድ ሱቁ እንደተከፈተ ቢታወቅ ደግሞ የታሪፍ ቅያሪው ከአስር ወራት በፊት መቀየር እንደነበረነት ይነገራቸዋል።
ነገር ግን አቶ መንግስቱ ለአንድ ንግድ ቤት ተብሎ ቀሪዎቹ አምስት መኖሪያ ቤቶች በታሪፍ አሰራሩ ወደ ንግድ ቤት የተጠቃለሉበት ሁኔታ ግርታን ፈጥሮባቸዋል። እንደ እርሳቸው ተመሳሳይ ችግር ያለባቸው የተለያዩ የንግድ ቤት የያዙ መኖሪያ ቤት ባለቤቶችን አነጋግረው ንግድ ቤት ላይ የቆጣሪ አነባበቡ የተለየ ስለሚሆን ከመኖሪያ ቤት ተመሳሳይነት ላለው የኤሌክትሪክ ፍጆታ በመጠን ከፍ ያለ ክፍያ መፈጸም የተለመደ መሆኑ ይነገራቸዋል።
ወይዘሮ እስከዳር አሊ ደግሞ አንድ መኖሪያ ቤት ያላቸው ቢሆንም በግቢያቸው ውስጥ ሁለት ንግድ ቤቶች አከራይተዋል። ንግድ ቤቶቹን ያከራዩት ከሁለት አመታት በፊት ቢሆንም የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን የሚከፍሉት በካርድ በሚሰራ የቆጣሪ መሳሪያ በመሆኑ ተከራዮቻቸው ወጪውን ይሸፍናሉ። በመሆኑም በተከራዮች ለሚሞላው የኤሌክትሪክ ክፍያ መጠን መጨመርና መቀነስ አሳስቧቸው አያውቅም። ነገር ግን ተከራዮቻቸው የፍጆታ ክፍያ መጨመር ላይ ቅሬታ አንስተው ስለማያውቁ በእርሳቸው ስም በተመዘገበው ቆጣሪ ምክንያት አድርገው በኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ቀርበው ጥያቄ አቅርበው አያውቁም።
የአቶ መንግስቱን ቅሬታ ሲሰሙ ግን 'አዲስ አሰራር ተዘርግቶ ይሆን' የሚል ሃሳብ ገብቷቸዋል። ተከራዮችም ይህን አይነት ያልተጣራ ወሬ ጆሯቸው ከደረሰ በኋላ ወጪውን ለማካካስ በሚል የሽያጭ እቃዎቻቸው ላይ ጭማሪ ስለማድረጋቸው ማጣራት እስካልተደረገ ድረስ ማንም እርግጠኛ መሆን ይከብደዋል።
የአሰራር ሁኔታውን ለማጣራት ወደ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ገብረእግዚያብሄር ታፈረ ደወልን። እርሳቸው እንደሚናገሩት፤ በአገሪቷ ውስጥ ምንም አይነት የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ ጭማሪ የለም። የሚቀየር የክፍያ አገልግሎት አሰራር ቢኖር እንኳን በመንግስት ደረጃ ፍቃድ ተደርጎበትና ለህብረተሰቡ በይፋ ተገልጾ እንጂ በድብብቆሽ የሚከናወን ጉዳይ አይኖርም። በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ ዝቅተኛ በሚባል ዋጋ እየቀረበ ይገኛል። ደንበኞቹ የሚያነሱት ጉዳይ ከአጠቃቀም ለውጥ ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ እና ከቆጣሪ ብልሽት ጋር ተያይዞ የተከሰተ ስለመሆኑ በቅድሚያ ማጣራት ያስፈልጋል። ነገር ግን በመኖሪያ ቤቱ ግቢ ውስጥ የንግድ ቤት ያለው ሰው በጋራ ለሚጠቀምበት ቆጣሪ እዲከፍል የሚጠየቀው የአገልግሎት ክፍያ ለመኖሪያ ቤት ከሚጠየቀው ጋር ሲነጻጸር ልዩነት አለው።
ለቤት አገልግሎት የሚጠቀሙት ላይ እስከ 50 ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ ፍጆታ ድረስ ሲገለገሉ በኪሎ ዋት 0 ነጥብ 273 ሳንቲም እንደሚጠየቅ ይጠቁማሉ። ከ50 ኪሎ ዋት በላይ ሲጨምር ግን የክፍያ ስሌቱ የመጨመር አዝማሚያ /progressive/ ባህሪ እንዳለው ያስረዳሉ። የንግድ ቤቶች ላይ ደግሞ እስከ 50 ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ ፍጆታ ድረስ ሲገለገሉ 0 ነጥብ 6088 ሳንቲም እንዲከፍሉ ይደረጋል። ፍጆታው በንግድ ቤቶች ላይ ከ50 ኪሎ ዋት ሲበልጥ ግን የክፍያ ስሌቱ አጨማመር አነስተኛ /semi progressive/ እየሆነ እንደሚሄድ ይገልፃሉ
እንደ አቶ ገብረእግዚአብሔር ማብራሪያ፤ የመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በሚገኝ የንግድ ቤት ምክንያት የኤሌክትሪክ ክፍያ ስሌቱ ጨምሯለ የሚል ቅሬታ ያላቸው ሰዎች ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የቆየ ስሌት በመሆኑ ምንም የተፈጠረ አዲስ አሰራር አለመሆኑን ማወቅ ይገባቸዋል። ለቤት አገልገሎት ሲሰራበት የነበረው የግለሰቦች ቆጣሪ የንግድ ቤት በመክፈታቸው ምክንያት ወደ ንግድ እንዲዞር ይደረጋል። ነገር ግን ለንግድ ቤቱ እና ለመኖሪያ ቤታቸው ባስገጠሙት አንድ ቆጣሪ ምክንያት ሁሉም ክፍያ በንግድ ቤት የቆጣሪ ስሌት ተጠቃሎብኛል የሚል ቅሬታ ያላቸው ሰዎች በህጋዊ መንገድ የተለያየዩ ቆጣሪዎችን በማስገጠም መጠቀም ይኖርባቸዋል። ለንግድ ቤቱ እና ለመኖሪያ ቤታቸው የተለያየ ቆጣሪ ከፋፍለው የሚጠቀሙ ከሆነም የመኖሪያ ቤቶቹን ኤሌክትሪክ ክፍያ በአነስተኛ ታሪፍ ሊጠቀሙ ይችላሉ።

የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ጀማነህ ፍርድ


የኦሮሚያ ጸረ ሙስና ኮሽን በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቶባቸው የነበሩት በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ጀማነህ የስድስ አመት ጸሁ እስራት ተፈረደባቸው።
በፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትናንትና በዋለው ችሎት በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ጀማነህ እና ቤተሰባቸውን ጨምሮ በ12 ሰዎች ላይ በተመሰረተው ክስ ላይ ብይን ሰጥቷል። አንደኛ ተከሳሽ አቶ ዘላለም ጀማነህ ላይ ምንጩ ያልታወቀ ሃብት በማፍራት፤ ያልታወቀ ሃብትን እውነተኛ በማስመሰል መሞከር እና ሃሰተኛ የመንግስት ሰነዶችን ህጋዊ በማስመሰል ጥቅም ላይ ማዋል በሚሉ ሶስት ክሶች ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ አድርጓቸዋል። በተከሳሹ ላይም የስድስት አመት ጸኑ እስራት እና የ11 ሺ ብር ቅጣት አስተላልፏል። ለቅጣት ማቅለያነት ከተቀመጡ ምክንያቶች ውስጥ ተከሳሹ ከዚህ በፊት ከማንኛውም ወንጀል ነጻ እንደነበሩ እና በመንግስት ካፍተኛ ኃላፊነት ላይ ያገለገሉ እንዲሁም የተለያዩ የጤና ችግሮች እንዳለባቸው የህክምና ማስረጃ ማቅረባቸውን በፍርድ ወቅት ተገልጿል።
በፍርድ ብይኑ መሰረት፤ ከከባድ ሙስና ወንጀሉ ጋር በተያያዘ በአዲሰ አበባ ኮልፌ ክፍለ ከተማ የሚገኝ መኖሪያ ቤት እና መኪና እንዲሁም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሚገኝ ኮንዶሚኒየም ቤትን ጨምሮ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ የነበሩ የተከሳሽ ገንዘብ ወደ መንግስት ገቢ እንዲሆኑ ተወስኗል።
ፍርድ ቤቱ በአቶ ዘላለም የቀድሞ ባለቤትና በሁለተኛ ተከሳሽ ላይ የቅጣት ማቅለያዎችን በመመልከት በነጻ አሰናብቷቸዋል። አንደኛ እና ሁለተኛ ተከሳሾች አሁን ላይ የተፋቱ መሆኑን ጠቅሶ ሁለተኛ ተከሳሽ ልጆቻቸውን ለማሳደግ በእናትነታቸው ሃላፊነት እንዳለባቸው በመጠቆም በነጻ ሲለቀቁ እስከ ሁለት አመት ድረስ በማንኛውም ወንጀል ተሳታፊ ሆነው ከተገኙ ግን አምስት አመት የሚደርስ እስራት እንደሚጸናባቸው ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ተገልጿል። ከሶስተኛ እስከ አምስተኛ እንዲሁም ስምንተኛ እና ዘጠነኛ ተከሳሾን በተመለከተ እስከ አምስት አመት በሚደርስ የተለያየ የእስር ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል ህዝባዊ አመጽ ምክንያት ከስልጣናቸው የተነሱት እና በስተኋላም በሙስና ወንጀል የታሰሩት አቶ ዘላለም ጀማነህ እና ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ 12 ግለሰቦች ላይ 14 ክሶችን መስርቶ ከአንድ አመት በላይ መረጃዎች ሲጣሩ ቆይተዋል።
የቀድሞው የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የክልሉ የግብርና ቢሮ ኃላፊ ሰኔ 2 ቀን 2008 . አስቸኳይ ስብሰባ ባደረገው የጨፌ ኦሮሚያ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ከተደረገ በኋላ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉ የሚታወስ ነው። የክልሉ መንግስትና ድርጅት አመራር በነበሩበት ወቅት የመንግስት እና የህዝብ ንብረቶችን በስማቸው በማዞር፣ በህግ ወጥ መንገድ ያገኙትን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ መያዝ እና ከገቢ በላይ ሀብት ማፍራት የመሳሰሉትን ከክሶቹ መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

ሁለት ጊዜ የደረቀው ሃይቅ - ሐሮማያ


ሐይቆች በተለያየ ምክንያት ይደርቃሉ። በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው የሐሮማያ ሐይቅ ደግሞ ከሌሎች ውሃ አካላት በተለየ ሁናቴ ሁለት ጊዜ ደርቋል። ለዚህ ምክንያቱ ምንድን ነው? ሐይቁን መልሶ ለማግኘት ምን ያስፈልጋል


በሐሮማያ ዪኒቨርሲቲ የአግሮኖሚ መምህር ዶክተር የሆኑት አብዱለጢፍ አህመድ ፤ ሐሮማያ ሃይቅ ሰባት ኪሎሜትር የሚሸፍን ርዝመት እና 14 ሜትር ጥልቀት የነበረው ሃይቅ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ሜዳ ሆኖ ውሃው ሊደርቅ የቻለው በአንድ ጊዜ የመጣ ክስተት አለመሆኑን ይናገራሉ። ከጊዜ ወደ ጊዜ ምህረት የለሽ እና ቁጥር የሌለው የውሃ ብዝበዛ ሲካሄድበት ቆይቶ ከአምስት አመታት በፊት ሃይቁ መድረቁን ይገልጻሉ። በአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በርካታ ውሃ ከሃይቁ እየተጠቀሙ ውሃው ሲቀንስ እና ሃይቁ በደለል ሲሞላ የእርሻ ቦታቸውን ወደ ሃይቁ እያስጠጉ መሄዳቸውንም ያስረዳሉ። በመቀጠልም የሃይቁን ድንበር ጥሰው ደለሉ ላይ ምርት በመጀመራቸው ውሃ እንዳይተኛ አይነተኛ ምክንያት መሆኑን ይጠቁማሉ።
እንደ መምህር አብለጢፍ ገለጻ፤ በቀጣይ ህብረተሰቡን በማስተባበር እና ስለ ውሃ አጠቃቀም ያላቸውን እውቀት በመጨመር የሚገኘውን ውሃ በቁጠባ እንዲጠቀሙ ማድረግ ይገባል። አርሶአደሮቹም ለእርሻ ስራቸው የጠብታ መስኖ እንዲጠቀሙ ጥብቅ እገዛ ማድረግ ያስፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪ አምራቾቹ በእያንዳንዳቸው እርሻ ውስጥ የሚቆፍሩትን የጥልቅ የውሃ ጉድጓድ በማስቀረት በአንድ ጉድጓድ ለጋራ እንዲጠቀሙ በማድረግ የከርሰምድር ውሃውን ብክነት መቀነስ ይገባል። ይህም ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጣው ጎርፍ አሰባስቦ ሃይቁ ቦታ ላይ እንዲቆይ ለማድረግና ተከማችቶ የቆየ የመሬት ውስጥ ውሃ ወደ ላይኛው የመሬት አካል እንዲወጣ ለማድረግ ያግዛል። ይህ ስራ በቀጣዮቹ አመታት በቁጥጥር ከተሰራ ሃይቁ መልሶ የማይመጣበት ምክንያት የለም። የሃይቁን መልሶ መሙላት የሚወስደውን ጊዜ ለመገመት ግን የዝናብ ሁኔታው ወሳኝነት አለው። ድርቅ ተደጋግሞ የሚከሰት ከሆነ የሃይቁ መፈጠር ሊራዘም ይችላል።
የሐሮማያ ተፋሰስ ልማት መልሶ የማልማት ቴክኒክ አስተባባሪ አቶ ተፈሪ ታደሰ እንደሚናገሩት፤ ለሐረማያ ሃይቁ መጥፋት በመንስኤ የሆነው ዋነኛ ምክንያቱ የአካባቢው መሬት መራቆት ነው። በተጨማሪም የመሬት አጠቃቀም ለውጥ ለውሃው መመናን አስተዋጽኦ አድርጓል። ለማሽላ፣ ለጥራጥሬ እህሎች እና ለፍራፍሬ የሚውል የነበረ የአካባቢው መሬት ለጫት ምርት እየዋለ ይገኛል። የምርት አይነቱ በአንደ ጊዜ በመቀየሩም ምክንያት የአፈር እጥበቱ በከፈተኛ ሁኔታ ጨምሯል። በአካባቢው የሚሸረሸረው አፈር ደግሞ በቀጥታ ወደ ሃይቁ በመግባት ከተቀመጠ በኋላ የሃይቁን ውሃ ቦታ ይዟል። በመሆኑም በአሁኑ ወቅተ በቦታው ላይ ደለል እንጂ የውሃ አካል አይገኝም። ከዚህ በተጨማሪ በአካባቢው እየተስፋፋ የመጣው የጫት ተክል ለማደግ በርካታ ውሃ የሚያስፈልገው በመሆኑ የሃይቁን ውሃ በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውል በር ከፍቷል። ይህም የሃይቁን ውሃ በማመናመን እንዲደርቅ ምክንያት ሆኗል። 
 
ከሶስት አመታት በፊት የደረቀው የሃሮማያ ሐይቅ መልሶ ውሃ እንዲይዝ ለማድረግ ፕሮጀክት ተነድፎ ነበር። በሃይቁ አካባቢ የሚገኘው የላይኛው የተፋሰስ ክፍል ላይ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራ ዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። በዚህ ውስጥ አካባቢውን መልሶ የማልማት እና የውሃ ሃብት አጠቃቀም ላይ ውጤታማ ስራዎች በተወሰነ ደረጃ ማከናወን ተችሏል። የመጀመሪያው ሃይቅ በተፈጥሮ የነበረና እና ጥልቀት ያለው ሲሆን ከደረቀ በኋላ መልሶ ለማልማት በተደረገው ጥረት አነስተኛ ውሃ በክረምት ወቅት እንዲይዝ ተደርጎ ነበር። ነገር ግን ያለው የውሃ አጠቃቀም የተዛባ በመሆኑ ለሁለተኛ ጊዜ እንዲደርቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። መልሶ ውሃ እንዲይዝ ለሚደረገው ጠረትም ውሃውን ከአቅሙ በላይ የመጠቀም ልምድ ሊስተካከል ይገባል። በመሆኑም ዋነኛው መፍትሄ የአካባቢውን የጫት ምርት በሌሎች ተችሎች በመቀየር የተመጣጠነ የውሃ አጠቃቀም ስርዓት እንዲስፍን ማድረግ ይገባል። በዚህም ከስድስት መቶ ሄክታር በላይ የሆነውን የሃይቁን ይዞታ መልሶ በማልማት ውሃ እንዲዝ ማድረግ ይቻላል። በአግባቡ ከተሰራም በአምስት እስከ አስር አመታት ባሉት ጊዜ ውስጥ ሃይቁን መልሶ ማግኘት የሚቻልበት እድል ሰፊ ነው። በአካባቢው የሚገኘውን ጥንቄ ሃይቅን እንዲሁም ሃረጂቶ የተባሉ አነስተኛ ሃይቆች ተፈጥረዋል።
«ማንኛውም ተክል ውሃ ይፈልጋል ጫት ስለተተከለ ብቻ ከፍተኛ ውሃ ከሃይቁ ላይ ተወስዷል ብሎ መደምደም አይቻልም» የሚሉት ደግሞ በእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ታደሰ ናቸው። ጫት ከፍተኛ ውሃ ስለሚወስድ ለሃይቁ መድረቅ አስተዋጽኦ አለው ለማለት ጥናት እደሚያስፈልግ ይገልጻሉ። ነገር ግን የሃይቁ ውሃ የሚከማችበት ጉድጓዳማ ስፍራ በተለያዩ ደለሎች እየተሞላ ሲሄድ ውሃው የመያዝ አቅሙ እንደሚቀንስ ይገልጻሉ። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ከሐይቁ ዙሪያ የሚገኘው የላይኛው ተፋሰስ አካባቢ ለአፈር መከላት የተጋለጠ በመሆኑ እደተከሰተ ያስረዳሉ። በመሆኑም የተፋሰሱን የእጽዋት ሽፋኑን በማሳደግ እና በመንከባከብ በጎርፍ ወቅት አፈር ተሸርሽሮ ወደ ሃይቁ እዳይገባ መጣር ዋነኛ ተግባር መሆን እንደሚገባው ይጠቁማሉ።
እንደ አቶ ተፈራ ገለጻ፤ የአካባቢው ህብረተሰብ የአፈር መሸርሸርን የሚከላከሉ የግብርና ዘዴዎችን እና ቴክኖሊጂዎችን እዲጠቀም ማበረታታት አስፈላጊ ነው። ይህ ከተከናወነ ሃይቁ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጎድጓዳማው አካባቢ በአፈር እየተሞላ ወደ ዝርግ መሬት የሚቀየርበትን ሂደት ያስቀረዋል። ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ ወደ ሜዳነት የተቀየረው እና ውሃ ለመያዝ አስቸጋሪ የሆነው ደለላላ ቦታ ለማስተካከል በተለያዩ አማራጮች ከሃይቁ ቦታ ላይ ደለሉ ቦታ ዲለቅ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህም በዝናብ እና በጎርፍ የሚገኘውን ውሃ እዲጠራቀም ቦታ ይከፍታል።ሁለት ጊዜ የደረቀ ሐይቅ

Featured post

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

                    የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደር...