Thursday, April 14, 2022

የፖለቲካ ሰው የግል ሃሳብ የለውም፤የግል ሃሳቤ እያሉ ፌስቡክ ላይ የሚለጥፉትም ስህተት ነው

                                - መጋቤ ሃዲስ እሸቱ አለማየሁ

 

 

ፖለቲከኞች የመንግስት አሊያም የፓርቲያቸው ሃሳብ እንጂ የግሌ የሚሉት ሃሳብ ስለሌላቸው ፌስቡክ ላይ የግል ሃሳቤ እያሉ የሚጭኑት ነገር ማቆም አለባቸው ሲሉ መጋቤ ሃዲስ እሸቱ አለማየሁ ተናገሩ።

ፖለቲከኞች ፌስቡክ ላይ የግል ሃሳቤ እያሉ የሚጭኑት ሃሳባቸውን እንዳይኖራቸው እመክራለሁ ያሉት መጋቤ ሃዲስ የፖለቲካ አመራሮች እና የመንግስት ሹመኞች የግል ሃሳቤ ነው እያሉ ፌስቡክ ላይ የሚጽፉት ሃሳብ ህዝብን ለስህተት ይዳርጋል ብለዋል። 

ፖለቲከኞች እና አመራሮች የወከላቸውን ፓርቲና መንግስት ሃሳብ እንጂ የግል ሃሳባቸውን በአደባባይ ማራመድ የለባቸውም። 

HOME 1 – Absolute grid – Page 85 – Ethio Online

 

ለአብነት አንድ የከተማ መስተዳደር የግሌ የሚለው ሃሳብ ሳይሆን የወከለው መንግስትን ሃሳብ ስለሆነ የግል ሃሳቤ ነው እያለ ፌስቡክ ላይ መጻፍ አይኖርበትም ሲሉ ያስረዳሉ።

የግል ሃሳብ አለኝ የሚል የፖለቲካ አመራር ካለ ሃሳቡን ለባለቤቱ ወይም ለልጆቹ ይንገራቸው ያሉት መጋቤ ሃዲስ እሸቱ ፤ በግል ሃሳብ ሰበብ የፖለቲካ አስተሳሰብ መጫን ስሀተት መሆኑን ተናግረዋል። 

የግል ሃሳብ ካላቸውም ስራቸውን ወይም ፖለቲካ አባልነታቸውን ሲለቁ ማስተላለፍ አለባቸው የሚል ሃሳብ ያቀርባሉ። 

ካለበለዚያ ግን ፌስቡክ ላይ እየወጡ የግል ሃሳቤ እያሉ ህዝብን ማደናገራቸው ትርጉም የለውም፤ ለችግርም እየዳረገን ነው ሲሉ ተችተዋል። 

አሁን ላይ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለሚታየው ልዩነትን የሚያሰፋ እና ግጭትን የሚቀሰቅስ አካሄድ ከአጠቃቀም ችግር የመጣ መሆኑን ሊታወቅ ይገባል ሲሉም መልዕክት አዘል መረጃቸውን አጋርተዋል።
     

No comments:

Post a Comment

Featured post

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

                    የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደር...